Tuesday, August 20, 2019

ኢትዮ-ኤርትራ

የኤርትራ ማስታወቂያ ሚንስቴር በድረ-ገፁ ባሠራጨዉ መግለጫ እንደሚለዉ ሶስቱ መንግሥታት በኤርትራና በኢትዮጵያ መካከል የተጀመረዉን የሠላም ሒደት-በተለይ፣ የአፍሪቃ ቀንድን ባጠቃላይ ለማተራመስ እያሴሩ ነዉ። መግለጫዉ «እርባና ቢስ» ያላቸዉ እርምጃዎች ካታር በመደበችዉ ገንዘብና የዘመቻ አገልግሎት የሚቀነባበሩ ናቸዉ።

የባህር በር አልባ #Landlocked አገር መሆን አንዱ ጥቅም አለው ከተባለ ይኽው ከሀያላኑ ፍጥጫ ነጻ መሆን ነው። በዚህ የሀብታም ዓረብ አገራትና የሀያላኑ ሽኩቻ መድረክ ከመሆን እነ ጅቡቲና ኤርትራ ፤ ሱዳን፤ ሶማልያ አላመለጡም። በአንጻሩ ኢትዮጵያ ይህ ከመጋረጃው በስተጀርባ የቀይ ባህርን የመቆጣጠር ወይም የአረብ ባህር የማድረግ ውዝግብ ወይም ትግል አይመለከታትም ።

በቅርቡ ኤርትራ የቀይ ባህርን ጠረፍ ለመቆጣጠር የሚደረግ ያለችውን «የጥፋት መልዕክተኞች»  ያለቻቸዉን ቱርክን፣ ቀጠርንና ሱዳንን አውግዛለች። 

የቱርክ መንግሥት፤ በጎርጎሪያኑ 2019 መጀመሪያ ላይ ለማይታወቀዉ «የኤርትራ ሙስሊም ሊግ» ሊቀመንበር፣ የኤርትራ ዑለማ ሊግ/የኤርትራ ራቢጣ-አይ ዑለማ በሚል ሽፋን ፅሕፈት ቤት መክፈቱን ይጠቅሳል። መግለጫዉ እንደሚለዉ ከጥቂት ቀናት በፊት ካርቱም፣ ሱዳን በተደረገ ስብሰባ ላይ የተሳተፉ «ጥፋት አራማጅ» ሰዎችም በኤርትራና በኢትዮጵያ ላይ የጠብ አጫሪነት መልዕክት አስተላልፈዋል። ቀጠር የኤርትራ የቅርብ ወዳጅ፣ የኤርትራና የጅቡቲ ሸምጋይም ነበረች።የቀይ ባህርን የዓረብ ባህር ለማድረግ በሳዑዲ አረቢያ የሚመሩት የዓረብ መንግሥታት ከካታር ጋር ዉዝግብ ከገጠሙ ወዲሕ ግን ኤርትራ ካታርን ትታ ከሳዑዲ አረቢያ ጎን መቆሟን አስታዉቃለች። ቱርክ ባንፃሩ ቀጥር ዉስጥ ያላትን ጦር ሠፈር አጠናክራለች።

የዓለም የሕዝብ ቁጥር

መቀመጫውን በዋሽንግተን ዲሲ ያደረገው ፒው የጥናት ማዕከል ይፋ ያደረገው መረጃ እንደሚጠቁመው የኢትዮጵያ ሕዝብ ቁጥር በጎርጎሮሳዊው 2100 ዓ.ም. 294 ሚሊዮን ይደርሳል ,

በተጠቀሰው ጊዜ 527 ሚሊዮን ዜጎች የሚኖሯት ናይጄሪያ በሕዝብ ብዛት ከአፍሪካ ቀዳሚ ትሆናለች። ከአፍሪካ ዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ፣ ታንዛኒያ፣ አንጎላ፣ ኒጀር፣ ግብፅ እና ሱዳን የሕዝብ ቁጥራቸው በከፍተኛ ፍጥነት ከሚያድግባቸው ሃገራት መካከል ቀዳሚ ናቸው።

በመረጃው መሠረት የምሥራቅ አውሮጳ ሃገራት የሕዝብ ቁጥር በከፍተኛ ደረጃ ይቀንሳል። አልባኒያ፣ ሰርቢያ፣ ሞልዶቫ እና ቦስኒያ ሔርዝጎቪና በ2100 ዓ.ም. የሕዝብ ቁጥራቸው በከፍተኛ ደረጃ ከሚቀንስባቸው መካከል ይገኙበታል።

የዓለም ስነ-ሕዝብ ቀን በዛሬው ዕለት ሲከበር የተባበሩት መንግሥታትን ጨምሮ ዓለም አቀፍ ተቋማት የሕዝብ ብዛት መጨመር በሰው ልጅ አኗኗር እና በልማት እቅዶች ላይ ስለሚኖረው ጫና ግንዛቤ ለማስጨበጥ ይሠራሉ።

የተፈጥሮ ሐብት መመናመን፣ የሐብት ክፍፍል መዛባት፣ መሠረታዊ ግልጋሎቶች አለመሟላትን የመሳሰሉ ቀውሶች በሕዝብ ቁጥር መብዛት የበለጠ እንደሚጠናከሩ የተባበሩት መንግሥታት መረጃ ይጠቁማል።

How Africa Shaped the Christian Mind Rediscovering the Africa Seedbed of Western Christianity Thomas C

J. Scott HorrellJ. Scott Horrell . Oden Downers Grove, IL 2008-01-11 Oden brings his patristic expertise and focused studies in African Christianity to bear in this pioneering book. Oden is the retired Henry Anson Buttz professor of theology at the Theological School of Drew University and author of numerous works including The Rebirth of Orthodoxy (San Francisco: HarperSanFrancisco, 2003) and a three-volume Systematic Theology (Peabody, MA: Hendrickson, 2006). He is also the general editor of the twenty-nine-volume Ancient Christian Commentary on Scripture (Downers Grove, IL: InterVarsity Press, 1998- ), and the forthcoming Ancient Christian Doctrine series on the Nicene Creed. He was Dallas Seminary’s 2009 Griffith Thomas lecturer. How Africa Shaped the Christian Mind argues that the formative flow of early Christian thought was from south to north, rather than the commonly assumed belief that Christianity is a European transplant on African shores. Oden sets forth seven ways that African Christianity informed Western and world Christianity: (1) the Western concept of the university; (2) Christian exegesis of Scripture; (3) early Christian doctrine (Tertullian, Origen, Cyprian, Athanasius, Augustine); (4) modeling conciliar patterns for ecumenical decision-making; (5) birth and development of monasticism; (6) Christian Neoplatonism; and (7) the development of rhetorical and dialectical finesse. The book asserts the indigenous nature of African Christianity that developed along the Nile and Medjerda valleys and extended through Ethiopia and Sudan, possibly moving southward into sub-Sahara Africa through Bantu migration. Repeatedly the author affirms that “African Christianity has arisen out of distinctly African experience on African soil” (p. 13), that is, North Africa is as fully African as is southern Africa (p. 79). Indeed, the very term “Africa” was first applied to the Tunisian peninsula and gradually evolved to include the entire continent. Oden invites a new wave of scholarship regarding African Christianity in that much is literally buried under the sand or may exist deep within sub-Sahara African traditions. It is easily forgotten that Alexandria was once the intellectual center of the world and a major location for both Jewish and Christian populations. The work opines that now is the time for the recovery of African orthodoxy, especially given the rapid expansion of African Christianity, the new hunger for intellectual depth, and “the perceived might of the Muslim world, coupled with the exhaustion of modern Western intellectual alternatives” (p. 101). Besides hoping for a renewed African orthodoxy rooted in its early fathers, Oden suggests that Christianity be reconciled with Islam, at least in the sense of “setting more realistic parameters of the tests that Christians face with Islam” (p. 134). Speaking of government intimidation of Christians in North Africa, Oden writes that Christians must “be protected by law, by police security and if necessary by proportional means of guaranteeing freedom of religion” (p. 136). With these various factors the author sets forth a tentative agenda for a consortium of scholars (especially African scholars) to plumb afresh the riches of the African heritage. The book includes an appendix that traces African Christian development from Mark (the apostle to Egypt) and Apollos (Acts 18) onward to Philotheos, patriarch of Alexandria in A.D. 1000. An excellent bibliography and six maps are helpful in visualizing the locations of Nilotic and Numidian Christian centers. How Africa Shaped the Christian Mind is a helpful challenge to consider the primacy of African theology in the first centuries of the church. Repeatedly Oden chides academics for its Eurocentric assumptions. “Even black nationalist advocates who have exalted every other conceivable aspect of the African tradition seem to have consistently ignored this patristic gift lying at their feet” (p. 11). Such repetition at times is belabored and, the point being made, detracts from the fertile content of the work. Yet the author’s intent is to encourage the nearly half billion African believers. Oden also recognizes the current lack of evidence to affirm Africa as a primary seedbed of Christianity. Given the centuries of interplay between Alexandria, Athens, Palestine, Carthage, and Rome, acute readers will wonder if the case that North African theology was distinctly African may be overstated. Yet this book is a very good beginning to what Oden sees as a multigenerational task. Christian workers focused on Africa and the Middle East will find it most helpful. Book reviews are published online and in print every quarter in Bibliotheca Sacra. Subcribe Today J. Scott Horrell J. Scott Horrell Professor of Theological Studies, Dr. Scott Horrell was born in Wenatchee on the Columbia River and grew up in Ephrata and Quincy in central Washington State. He is a graduate of Seattle Pacific University. He has pastored five times, twice in urban Brazil. Now he has enjoyed 22 years at DTS with about the same number of years in ministry outside the US, centered on teaching Bible doctrine, theology, church planting, and pastoral training. He is currently an adjunct professor of doctoral studies at SETECA in Guatemala, and occasional adjunct professor at others schools in various parts of the world. He and his wife Ruth are grateful for their two daughters, two son-in-laws, and eight grandchildren. Review Jul 21, 2018 D. Scott BarfootD. Scott Barfoot Teams That Thrive: Five Disciplines of Collaborative Church Leadership. One of the greatest theological insights embodied in the triune God, the biblical institution of marriage, and the local church is the worship-inspiring and transformational... Review Jul 21, 2018 Joseph D. FantinJoseph D. Fantin Acts: An Exegetical Commentary. Volume 4: 24:1–28:31. Now complete, Craig Keener’s four volume, 4501 page (xlii + 4459), 10¾ inch (27.5 cm) wide, 19 lb (8.62 kg) commentary, with more than 45,000 ancient nonbiblical references on... Arts & Media Jul 9, 2019 Patrick ThomasPatrick ThomasRyan FlaniganDarrell L. BockMikel Del Rosario Generational Unity in Worship Music - Classic Spiritual Life Jul 3, 2019 Daniel L. HillDaniel L. Hill The Names We Call Ourselves Dr. Daniel Hill, assistant professor of Theological Studies, highlights of the primary tasks of the people of God, which is to remember how identity is defined by relationship to... Theology Jul 2, 2019 Daniel DarlingDaniel DarlingDarrell L. Bock Human Dignity and Cultural Engagement Spiritual Life Jun 28, 2019 Mark L. BaileyMark L. Bailey Alive to Forward To put it in a simple metaphor, before we came to Christ, the Bible teaches that all of our life was a life of driving in reverse. The doctrine of depravity doesn’t teach that... DTS Voice offers biblically-centered articles, stories, podcasts, and points of view from the DTS family designed to encourage and equip the church for gospel transformation. Sign up for DTS voice updates Copyright Dallas Theological Seminary -- Sent from Fast notepad

ጣይቱ ብጡል ሃይለማርያም ብርሃን ዘኢትዬጵያ (ከ ነሐሴ 12: 1832 - የካቲት 4: 1910)

በአመራር ጥበባቸው አቻ ያልተገኘላቸው ንግስት
በሃገራችን የመጀመሪያው ባንክ # Bank of Abyssinia የተቋቋመው
በእንግሊዞች ነበር። ባንኩ ለስራ ማስኬጃ የተበደሩ ደንበኞች ብድራቸውን
መክፈል ሳይችሉ ሲቀሩ ንብረታቸውን ይወርሳል ከዚያም ይከሳል አልፎ ተርፎ
ተበዳሪወቹም ለእስር ይዳረጋሉ።
ታዲያ ይሄ ጉዳይ እቴጌ ጣይቱን እጂጉን ያሳስባቸው ነበርና
አንድ ቀን አፄ ሚኒሊክ እና ሹማምንቱ በቤተ መንግስቱ እልፍኝ ተሰብስበው
ስለ ባንኮ ኦፍ አቢሲኒያ ሲወያዩ እቴጌ ጣይቱ ሃሳብ አቀረቡ
"በመናገሻ ከተማችን ህዝባችንን እስር ቤት አዘጋጂቶ አይናችን እያየ
ጆሮአችን እየሰማ የእንግሊዝ መንግስት ያሻውን እንዲህ ሲሰራ ይሄ ህዝብ
ምኑን የእኛ ነው ማለት ይቻላል? ግብርስ መከፈሉ ፋይዳው ምንድን ነው?
እነዚህ ባለእዳ ተብለው በገዛ አገራቸው ፍዳቸውን ለሚያዩት # ሰወቻችን
እዳቸውን የሚከፍሉበት መፍትሄ ልናበጅላቸው አይገባምን?" ብለው ጠየቁ
እና እቴጌም ባንክ እንዲቋቋም መፍትሄ አቀረቡ ሹማምንቱም በእቴጌ ሃሳብ
ተስማሙ ተፈቀደላቸውም።
ባንክ በሚል ስያሜ # የእቴጌ_ጣይቱ_የእርሻና_ንግድ_ማስፋፊያ_ማህበር
ተቋቋመ ==>> የአሁኑ የ # ልማት_ባንክ መሰረት የተጣለው ያኔ በእቴጌይቱ
ነበር
- የመጀመሪያውን 100,000 ብር እቴጌ ጣይቱ
- ከመንግስት ግምጃ 200,000 ብር
ሌላውን አክሲዬን ደግሞ
- ንጉስ ወልደ ጊወርጊስ
- ራስ ተሰማ ናደው
- ንጉስ አባ ጂፋር
- እና ሌሎች የመንግስት ሹማምንት
- እና ታዋቂ የሮዝንደር ነጋዴወች እንዲያወጡ አደረጉ
ቀሪውን አክሲዬን ደግሞ
- ህዝቡና መሳፍንቱ ገዛ::
በመስከርም 2 /1909 ዓም ባንኩ ስራ ጀመረ።
ባንኩ ስራ እንደጀመረ ባንክ ኦፍ አቢሲንያ ላሰራቸው ሰወች በማበደር ከእዳ
እና እስራት ነፃ አደረገ።
ለንግድና እርሻ ማስፋፊያ የሚሆን ብድር በመስጠት የህዝቡን የኢኮኖሚ
እድገት ማበልፀግ ተቻለ።
በእቴጌ ጣይቱ የተሾሙ የበንኩ ስራ አስኪያጂ
~ የመጀመሪያው ነጋድራስ በሃብቴ
~ ቀጥሎ አቶ ምትኬ
~ ለጥቆ አቶ ይታጠቁ ነበሩ

Tuesday, July 23, 2019

አረንጓዴ_አሻራ

ንግድና ኢንዱስትሪ ሚኒስቴርና በሚኒስቴሩ ስር የሚገኙ 15 ተጠሪ ተቋማት በቦሌ ለሚና በቂሊንጦ ኢንዱስትሪ ፓርክ ሐምሌ 15/2011 የችግኝ ተከላ አካሄዱ፡፡

ከ3,800 በላይ ሠራተኞች በተሳተፉበት በዚህ የችግኝ ተከላ ከ22,000 በላይ ችግኞችን በቦሌ ለሚና በቂሊንጦ ኢንዱስትሪ ፓርኮች ለመትከል ተችሏል፡፡

በቂሊንጦ ኢንዱስትሪ ፓርክ በነበረው የቸችግኝ ተከላ መርሃ ግብር የተሳተፉት የንግድና ኢንዱስትሪ ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ አቶ ተካ ገብረየሱስ እንደገለፁት ይህ የችግኝ ተከላ መርሃግብር በዋናነት የአረንጓዴ ኢኮኖሚ ግንባታ አቅም መፍጠሪያና በሐምሌ 22/2011 የሚካሄደው ሀገራዊ የአረንጓዴ አሻራ ቀን መንደርደሪያ ነው ብለዋል፡፡

ሐምሌ 22 ለሚካሄደው ሀገራዊ የችግኝ ተከላ ሁሉንም የሚኒስቴር መስሪያ ቤቱና ተጠሪ ተቋማት ሠራተኞችን ማሳተፍ እንዲቻል የቅድመዝግጅት ስራዎች መጠናቀቃቸውን አውስተው በእለቱም በኦሮሚያ ክልል በፍቼ ከተማ አካባቢ 80,000 ችግኞች እንደሚተከሉ ገልፀዋል፡፡

በችግኝ ተከላው የተሳተፉ ሠራተኞች እንደገለፁት በዚህ ሀገራዊ የአረንጓዴ አሻራ ቀን ላይ የራሳቸውን አሻራ ለማሳረፍ በመቻላቸው የተሠማቸውን ደስታ ገልፀው በሀገራዊው የሠላም፣ የዴሞክራሲና የልማት እንቅስቃሴም ውስት ሁሉም በላፊነት የየግሉት አስተዋፅኦ በማድረግ የተጀመረውን ሀገራዊ መግባባት ማሳደግ እንደሚገባም ገልፀዋል፡፡

Friday, July 12, 2019

ወደ ኋላ የመመለስ ስጋት

ኢትዮጵያ ጋዜጠኞችን በማሰር፤ የጸረ-ሽብር ሕጓን መልሳ ሥራ ላይ በማዋል እና የኢንተርኔት ግልጋሎትን በማቋረጥ ወደ ቀደመው የመገናኛ ብዙኃን ነፃነት አፈና የመመለስ አደጋ እንደተጋረጠባት የጋዜጠኞች መብት ተቆርቋሪ ድርጅት ፣ (CpJ ) አስጠነቀቀ።

በአሁኑ ወቅት በትንሹ ሦስት ጋዜጠኞች በእስር ላይ እንደሚገኙ የጋዜጠኞች መብት ተሟጋቹ ሲፒጄ (CPJ) አስታውቋል። ሌሎች ሦስት ጋዜጠኞች ታስረው ቢፈቱም አሁንም የፍርድ ቤት ሙግት እንደሚጠብቃቸው ከሰሐራ በታች የሚገኙ የአፍሪካ ሃገራት የድርጅቱ ተወካይ ሞቶኪ ሙሞ ለዶይቼ ቬለ ተናግረዋል።

ሞቶኪ ሙሞ እንደሚሉት ኢትዮጵያውያን ጋዜጠኞች ሥራቸውን በአግባቡ ለመከወን ፈተና በዝቶባቸዋል።
ሞቶኪ ሙሞ «ባለፈው ሰኔ የኢንተርኔት አገልግሎት መቋረጡ የመገናኛ ብዙኃን ነፃነትን እጅግ ጎድቷል።

ጋዜጠኞች ሥራቸውን ለመሥራት፣ ከመረጃ ምንጮቻቸው ለመገናኘት፣ መረጃዎቻቸውን ለማጣራት ሰበር ዜናዎችን በፍጥነት ለማተም ፈተና ሆኗል። በግንቦት እና በሰኔ ወራት የታሰሩ ጋዜጠኞች አሉ።

ቢያንስ አንድ ጋዜጠኛ እና ባልደረባው በሥራቸው ሳቢያ ክስ ተመስርቶባቸዋል። በቅርቡ ከዚህ ቀደም ለመገናኛ ብዙኃን ብዙ ችግር ሲፈጥር በቆየው የጸረ-ሽብር ሕግ ጋዜጠኞች መታሠራቸውንም ደርሰንበታል።» ብለዋል ።

የጋዜጠኞች መብት ተሟጋቹ ያነጋገራቸው ኢትዮጵያውያን ባለሙያዎች እና የሰብዓዊ መብት ተሟጋቾች ባለፈው አንድ ዓመት የመገናኛ ብዙኃን ነፃነት መሻሻል ቢያሳይም የመንግሥቱ የቀደሙ ልምዶች የማገርሸት ምልክት ማሳየታቸውን ተናግረዋል።

የጠቅላይ ምኒስትር ዐቢይ አሕመድ መንግሥት በጀመራቸው ማሻሻያዎች ለውጥ ይደረግበታል የተባለው የጸረ-ሽብር ሕግ መልሶ ጋዜጠኞችን ለማሰር ግልጋሎት ላይ መዋሉ አሳሳቢ መሆኑን ጠቁመዋል። ሞቶኪ ሙሞ «አዎንታዊ መሻሻል ወደታየበት፣ መንግሥት ጋዜጠኞችን ወደማያስርበት እና ኢትዮጵያ የመገናኝ ብዙኃን ነፃነት የተከበረባት አገር ትሆን ዘንድ ሊያረጋግጥ ወደሚችለው የማሻሻያ እርምጃ እንመለስ ማለት እንፈልጋለን።

በእርግጥ የመገናኛ ብዙኃን ነፃነት መፃኢ እጣ-ፈንታ አሳስቦናል፤ የዛኑ ያህል የታዩ ለውጦችንም እንረዳለን። የምናነሳቸው አሳሳቢ ጉዳዮች ምላሽ አግኝተው ኢትዮጵያ የመገናኛ ብዙኃን ነፃነት የተከበረባት አገር ትሆናለች ብለን ተስፋ እናደርጋለን።» ሲሉ በአጽንዖት ተናግረዋል።

የሰብዓዊ መብት ተሟጋቹ አምነስቲ Amnesty International  ኢንተርናሽናል የኢትዮጵያ መንግሥት እርምጃ አገሪቱ ባለፈው አንድ ዓመት ገደማ ያሳየችውን መሻሻል ሊቀለብስ እንደሚችል በትናንትናው ዕለት አስጠንቅቆ ነበር። ወደ ኅንላ እንዳንመለስ ጎበዝ።

Wednesday, July 10, 2019

ምን ሊሆን ይችላል

መፈንቅለ መንግስታት ያደረሱት የኢኮኖሚ ጉዳት
በቅርብ ግዜያት የተደረጉት መፈንቅለ መንግስታት ለኢንቨስትመንት ፀር ነው - በተለይም የውጭ ኢንቨስትመንት ፤ የቱሪዝም ፍሰቱን ይቀንሳል ። መፈንቅለ መንግስት ተደረገ የሚል ዜና መሰማት እንኳን የሀገርን ገፅታ በእጅጉ ይጎዳል ። ለዚሕም ምሳሌዎቹ በቱርክ ፤ በታይላንድ ፤ በግብፅ እና በሱዳን የትድረጉት ኣይነተኛ ምሳሌዎች ናቸው ።
ጃንሆይ እንኳን የተሞከረባቸውን የ53ቱን የነ መንግስቱ ንዋይን ሙከራ "የታህሣሡ ግልግር " ከማለት ውጭ  መፈንቅለ መንግስት ነው አላሉም።

Sunday, July 7, 2019

ራስ -ተፈርያውንና ጃንሆይ

‌«ወደ አህጉረ አፍሪካ ተመልከቱ አንድ ጥቁር ይነግሣል፤ ነፃነትም ይሆናል» ጃማይካዊው የመብት ታጋይ ማርከስ ጋርቬይ ነበር ይህን የተነበየው።  ኢትዮጵያን ከአራት አሥርት ዓመታት በላይ የገዙት ቀዳማዊ አፄ ኃይለ ሥላሴ በ1923 ዓ. ም. የንግሥና ዙፋናቸውን ጫኑ።

የእሳቸው ንግሥና ዜና አህጉረ አፍሪካን አልፎ ጃማይካ ደረሰ። ወሬውን የሰሙ የራስ ተፈሪ እምነት ተከታዮች ፈጣሪ በሥጋ ተገልጿ፤ ጠባቂያችን ነግሧል በማለት ወደ ኢትዮጵያ ጎረፉ። ራስ ተፈሪያን ጃህ እያሉ የሚጠሯቸው ጃንሆይ፣ በፈረንጆቹ 1966 ዓ. ም. ወደ ጃማይካ አቀኑ። ሥፍር ቁጥር የሌለው ሰው ተቀበላቸው። ባዩትም ነገር እጅግ ተደነቁ። እሳቸው ወደ ኪንግስተን ባቀኑ ጊዜ የሰማይ ውሃ ዓይንሽን ለአፈር ብሏት የነበረችው ጃማይካ በዝናብ እንደራሰችም ይነገራል።

የሬጌ ሙዚቃ ንጉሡ ቦብ ማርሌም በሙዚቃው አፍሪካን እና ኢትዮጵያን እንዲሁም ንጉሡን የመፃኢ ዘመን ተስፋ እና መጠጊያ አድርጎ ይስላቸው ነበር። ለአፍሪካ አንድነት በሠሩት ውለታ ሊታወሱ ይገባል ተብሎ በቅርቡ ሃውልት የቆመላቸው ጃንሆይም ወደ አፍሪካ መመለስ ለሚሻ ጥቁር ይሁን በማለት ሻሸመኔ አካባቢ 200 ሄክታር ገደማ መሬት ለገሱ።

የራስ ተፈሪ እምነት ተከታዮች ከደቡባዊ የአፍሪቃ ክፍል እስከ ምዕራቡ ጥግ፤ ከሰሜን እስከ ምስራቅ ይገኛሉ። እንደ ሻሸመኔ ግን ያለ አይመስልም።
መጀመሪያ ላይ 12 ጃማይካዊያን ብቻ ወደ ሻሸመኔ እንዳቀኑ ይነገራል። ኋላ ላይ ግን የትየለሌ ራስ ተፊሪያኖች ጉዟቸውን ወደ ሻሸመኔ አደረጉ።

አሁን ላይ ሻሸመኔ ውስጥ በርካታ የራስ ተፈሪ እምነት ተከታይ ጃማይካዊያን ይኖራሉ። አሁን ግን ትኩረቱ ከአራት አሥርት ዓመታት በላይ ከቆዩባት ሻሸመኔ ወደ ሐረር የዞረ ይመስላል። ለምን?

ከሻሼ ወደ ሐረር  ራስ እዝቄል ኩማ ለበርካታ ዓመታት ኢትዮጵያ ውስጥ የኖረ የራስ ተፈሪያን እምነት ተከታይ ነው። ኢትዯጵያ ውስጥ ወልዶ ከብዷል። ሕይወቱን መሥርቷል። ከሻሸመኔ ወደ ሐረር የሚደረገውን መንፈሳዊ ጉዞ የሚመራው ራስ እዝቄል ኩማ ለራስ ተፈሪያን ማሕበረሰብ ከሻሸመኔ ይልቅ ሐረር የተሻለ ቅርበት እንዳላት ይናገራል።

«ልንሆን የሚገባው ሐረር ነው። ጃህ፤ ንጉሳችን የተወለዱበት ሥፍራ ነው። እዚያ ኪዳነ ምሕረት ቤተክርስትያን አለች። እዚያ ነው እትብታቸው የተቀበረው» ይላል። እርግጥ ነው ይህን ጉዞ ለማድረግ ቆርጠው የተነሱ ራስ ተፈሪያኖች ጥቂት እንደሆኑ ራስ እዝቄል አይሸሽግም። መኖሪያቸውን ሐረር ያደረጉ ጃማይካውያን እንዳሉም ይናገራል።

«ጉዞው ለኛ ትልቅ ትርጉም አለው። ወደ ሐረር እንድንጓዝ የሚያደርግ መንፈሳዊ ጥሪ ደርሷል። ይህን ጉዞ እኛ ለመጀመር እናስበው እንጂ ጥሪው ለሁሉም የራስ ተፈሪያን እምነት ተከታዮች ነው።»

ራስ ኩማ ሐረር ለራስ ተፈሪ እምነት ተከታዮች ያላትን ሥፍራ ሲያስረዳ፤ «እኔ ሁሉም የራስ ተፈሪ እምነት ተከታይ በሕይወት ዘመኑ አንዴ ኤጀርሳ ጎሮን ቢያይ ደስ ይለኛል። የእስልምና እምነት ተከታዮች ወደ መካ እንደሚያቀኑት ሁሉ የኦርቶዶክስ እምነት ተከታዮች ቤተልሔምን ለማየት እንደሚጓጉት ሁሉ እኛም ሐረርን ማየት እንናፍቃለን» ይላል። ግን ግን የራስ ተፈሪ እምነት ተከታዮች ሐረር ውስጥ እንዴት ያለ ማሕበረሰብ ይሆን ለመመሥረት የሚሹት? ራስ እዝቄል ጉዞው ገና ጅማሮ ላይ ያለ ቢሆንም ልናቋቁም ያሰብነው ማሕበረሰብ ሻሸመኔ ከሚገኘው ለየት ያለ ነው ይላል።

«ለሁሉም የራስ ተፊሪያን እምነት ተከታይ የሚሆን ምቹ ሥፍራ እንዲሆን ነው ፍላጎታችን። እዚያ ከሚኖረው ማሕረበሰብ ተነጥለን የመኖር ዕቅድ የለንም። አንድነትን መሠረቱ ያደረገ፤ እርስ በራስ የሚከባበር እና የሚግባባ ማሕበረሰብ የመፍጠር ፍላጎት አለን።»
ከአርባ ዓመታት በላይ ጃማይካውያንን ያስጠለለችው ሻሸመኔስ ምን ይሰማት ይሆን? ራስ እዝቄል ጉዞው ከሻሸመኔ ጠቅልሎ ወጥቶ ወደ ሐረር የሚደረግ 'ፍልሰት' ተደርጎ እንዳይታሰብ ይሰጋል።

«ጉዳዩ አዲስ ምዕራፍ የመክፈት ጉዳይ ነው። በርካቶቻችን በምዕራብ ሃገራት ተጠልለን የምንኖር ነበርን። አሁን ግን አንድ የሚያደርገንን ነገር እንፈልጋለን። ይህን ስናስብ ደግሞ 'ጃህ' ከተወለዱበት ሥፍራ የተሻለ ቦታ የሚገኝ አይመስለኝም።»

ኤጀርሳ ጎሮ ጉዞው ጅማሬ ላይ ነው ያለው። ኤጀርሳ ጎሮ ላይ አንድ ቤተ - ክርስትያን የማነፅ ሥራ ከዕቅዱ መካከል ይገኛል። በሁለት ዓታት ጊዜ ውስጥ ብዙ ነገሮች ተሳክተው ጉዞ ሻሸመኔ - ሐረር የተሳካ እንደሚሆን ራስ እዝቄል እምነት አለው።

ከሐረሪ ክልል ባህል እና ቱሪዝም ቢሮ ጋር በትብብር እየሠሩ እንደሆነም ይናገራል። የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስትያን የምስራቅ ሐረርጌ ፅህፈት ቤት ጉዞው የተሳካ አንዲሆን ከራስ ተፈሪያኖች ጋር በጥምረት እንዲሰራ እንደሚፈልጉ ራስ እዝቄል ይጠቁማል። በመላው ዓለም የሚገኙ ራስ ተፈሪያኖች ለጉዳዩ ጆሮ መስጠት እንደጀመሩ የሚናገረው ራስ እዝቄል ቤተክርስትያን የማነፁን ሥራ እንዲሁም ሌሎች ተግባራት የሚጠናቀቁ ከሆነ እርዳታው ከዚያም ከዚህም መምጣቱ አይቀርም ባይ ነው።

ኤጀርሳ ጎሮ አዲሲቷ የራስ ተፈሪ እምነት ተከታዮች ትሆን ይሆን? በስተመጨረሻ የእምነቱ ተከታዮች የጃንሆይን የትውልድ ስፍራ መጠጊያቸው አድረርገው ኃይማኖታዊ ጉዟቸውን ወደ ተስፋይቱ ምድር ያደርጉ ይሆን? ።

Saturday, July 6, 2019

Sidama ክልል

የሲዳማን ክልልነት ጥያቄ የጠቅላይ ሚንስትር ዐቢይ መንግሥት በድርድር እንዲፈታው ዐለም ዐቀፉ የግጭት አጥኝ ቡድን አሳስቧል፡፡ ኢንተርናሽናል ክራይስስ ግሩፕ #ICG ከናይሮቢ ቢሮው ባወጣው ወቅታዊ ሪፖርታዥ መፍትሄው የሕዝበ ውሳኔውን ቀን በቶሎ ቆርጦ ማሳወቅ ነው ብሏል፡፡ ዞኑ በተናጥል ክልልነቱን ካወጀ ደሞ እንደ ሀዋሳ ያሉ አንገብጋቢ ጉዳዮች እስኪፈቱ የመንግሥት ምስረታውን እንዲያዘገየው መክሯል፡፡ ጉዳዩ በጥንቃቄ ካልተያዘ ደቡብ ክልል በሞላ ብጥብጥ ውስጥ ሊገባ ይችላል፤ ሕገ መንግሥታዊ ዝግጅት ሳይደረግ መንግሥት የሲዳማን ክልልነት ከተቀበለም ያው ግጭት ሊከሰት ይችላል ሲል አስጠንቅቋል፡፡ ሕዝበ ውሳኔው በጊዜ ገደቡ ካልተካሄደ በመጭው የፈረንጆች ሐምሌ 18 የሲዳማ ክልልን በተናጥል ለማወጅ ሲዳማ ዞን በያዘው አቋም እንደጸና ነው፡፡ በተያያዘ ዜና የሲዳማ እጀቶዎች ዛሬ ሃዋሳ ላይ ባደረጉት ስብሰባ የትኛውንም ኢ-ሕገ መንግሥታዊ ውሳኔ ላለመቀበል መወሰናቸውን የሲዳማ ዜና ምንጮች ዘግበዋል፡፡

Tuesday, July 2, 2019

የ ኢራን -አሜሪካን ውዝግብ ዚቅ

የኢራን አብዮት 40ኛ አመት ፥

ሻሁ የዘመናት አንፀባሪቂ ጀንበራቸዉ በ38ኛዉ ዓመት ከምዕራብ አድማስ ጥግ መድረሷን የተረዱት መሠለ።ጥር 1979 «ለዕረፍት» በሚል ሰበብ ጓዛቸዉን ጠቅልለዉ ከቴሕራን ዉልቅ አሉ።በወሩ የአመፁ በተለይ እስልምናን እንደ ርዕዮተ ዓለም አንግበዉ የሚታገሉ ወገኖችን--- ይመሩ የነበሩት ታላቁ አያቱላሕ ሩሆላሕ ኾሚኒ ከ16 ዘመን ስደት በኋላ ቴሕራን ገቡ ።

እስራኤል እንደ ሐገር ከተመሰረተች ከ1948 ጀምሮ የፀናዉ የመካከለኛዉ ምሥራቅ ፖለቲካዊ ሥርዓት ባዲስ ጎዳና ይሾር ገባ።ከ1917 (ዘመኑ በሙሉ እንደ ጎርጎሪያኑ አቆጣጠር ነዉ) ጀምሮ ዓለምን በኮሚንስት-ካፒታሊስት እሁለት ገምሶ የሚያናክሰዉ ርዕዮተ-ዓለም፣ እስላምን-ከአብዮት የቀየጠ ሰወስተኛ አስተሳሰብ ታከለበት።የካፒታሊስቱ ቁንጮ የዓለም ልዕለ-ኃይል ዩናይትድ ስቴትስ ሐብታም ታማኝ፣ታዛዥ ጥብቅ ወዳጅዋን አጣች።የፋርሶች የ2500 ዘመን ንጉሳዊ አገዛዝ ተገረሠሠ።

የዩናይትድ ስቴትስና የብሪታንያ ሰላዮች ከአንድ ዓመት በላይ ያሴሩ፣ያቀነባበሩ፣በሚሊዮን የሚቆጠር ዶላር የረጩበት የመፈንቅለ መንግስት ሴራ በድል ተጠናቀቀ።ዘመቻ አጃክስ ብለዉት ነበር። በ1951 በኢራን ሕዝብ የተመረጡት ጠቅላይ ሚንስትር መሐመድ ሞሳደጊ ከስልጣን ተወገዱ።የለንደን ዋሽግተን ታማኝ አገልጋይ ንጉስ መሐመድ ሬዛ ፓሕላቪ ሥልጣኑን ሙሉ በሙሉ ተቆጣጠሩ።

ለዴሞክራሲያዊ ሥርዓት ሲታገሉ የነበሩት ኢራኖች በጅምር ዴሞክራሲያዊ ሥርዓታቸዉ ቅጭት አንገታቸዉን ሲደፉ፣ ለለዲሞክራሲያዊ ሥርዓት ፅናት እንደሚታገሉ ጧት ማታ የሚደሰኩረት የለንደን-ዋሽግተን መሪዎች በሴራቸዉ ድል ይቦርቁ ገቡ።ደስታ-ፌስታዉ ወዳጅነቱን አጠንክሮ የዩናይትድ ስቴትሱ ፕሬዝደንት ቴሕራንን እንዲጎበኙ ምክንያት ሆኖ ነበር።

«ፕሬዝደንቱ ቴሕራን ሲገቡ ከሩብ ሚሊዮን የሚበልጥ ሕዝብ አቀባበል አድርጎላቸዋል።ለዚሕ ታሪካዊ ጉብኝት ሻሕ ፓሕላቪ ንጉሳዊዉ ቤተ-መንግስት ዉስጥ ልዩ አቀባበልና ለፕሬዝደንቱ ስጦታ አቅርበዉላቸዋል።»

ታሕሳስ 1959።

በርግጥም 1977፣ 1952 ወይም 53 ወይም 59 አልነበረም።ፕሬዝደንት ጂሚ ካርተርም አይዘናወርን አይደሉም።ካርተር በ1977 ማብቂያ ወደ ቴሕራን የተጓዙት ግን አይዘናወር በ1953 ከዙፋናቸዉ ከተከሏቸዉ፣ በ1959 ቴሕራን ድረስ ተጉዘዉ ከጎበኟቸዉ ከንጉሰ-ነገስት መሐመድ ሬዛ ፓሕላቪ ጋር የ1978ን አዲስ ዓመት ዋዜማን ለማክበር ነዉ።

ካርተር እንደ ልዕለ ኃያል ሐገር መሪ ቴሕራን ቤተ-መንግሥት ዉስጥ ሲንበሻበሹ በድፍን ኢራን፣  ዉስጥ ዉስጡን የሚንተከተከዉን ሕዝባዊ ብሶትና ቁጣ ያወቁት አይመስሉም።የዓለምን እንቅስቃሴ እያጮለገ ሰዓት-በሰዓት

ለመሪዎች ያቀርባል የሚባለዉ CIAም ሆነ ተባባሪዎቹ የብሪታንያዉ MI6 ወይም የእስራኤሉ ሞሳድ ለአሜሪካ መሪ የሰጡት መረጃ አልነበረም።ከነበረም ሰዉዬዉ ይፋ ማድረግ አልፈለጉም።

የፈለጉት ንጉሰ ነገስት መሐመድ ሬዛ ፓሕላቪ ለ37 ዘመን ረግጠዉ የገዟት ኢራን «የሰላም ደሴት» እንደሆነች ማወደስ ነበር።«ኢራን በሻህ ታላቅ አመራር ምክንያት፣ በዓለም እጅግ ከሚታወከዉ አካባቢ አንዱ በሆነዉ አካባቢ የመረጋጋት ደሴት ናት።ይሕ ሊሆን የቻለዉ፣ ግርማዊ ሆይ፣ በእርስዎ አመራርና ሕዝብዎ በሚሰጥዎ ክብር፣ አድናቆትና ፍቅር ምክንያት ነዉ።»

ካርተር ያንቆለጰሷቸዉ መሐመድ ሬዛ ፓሕላቪ የኢራን ንጉሰነገስ ናቸዉ።ሻሐንሻሕ፣ የአርያን ነገድ ብርሐን ናቸዉ።የኢራን ጦር ኃይሎች ጠቅላይ አዛዥ ናቸዉ።የኢራን ዘመናይ ሥርዓት መሥራች ናቸዉ።በ1979 በኢራን የአሜሪካ ኤምባሲ የፖለቲካ ጉዳይ ኃላፊ የነበሩት ማይክል ሜኪንኮ እንዳሉት ደግሞ ለአሜሪካኖችም ታማኝ አጋልጋይ ናቸዉ።«እሳቸዉ በኢራን የኛ ሰዉ ናቸዉ።የሳቸዉ ኢራን የኛ ሐገር ናት።ኢራን የነዳጅ ምንጫችን ናት።ኢራን የጦር መሳሪያ ደንበኛችን ናት።ኢራን በራስዋ መንገድ ከሶቭየት ሕብረት ጥቃት የምትከላከለን ናት።»

ሰዬዉ ለታማኞቻቸዉና ለሚታመኑላቸዉ በርግጥም ሁሉም ናቸዉ።ለአብዛኛዉ ኢራናዊ ግን ረጋጭ፣ጨቋኝ፣ ጨካኝ ናቸዉ።የ37 ዘመኑ ጭቆና ያንገሸገሸዉ ሕዝብ የአሜሪካዉ ፕሬዝደንት ቴሕራንን ከጎበኙ ከጥቂት ወራት በኋላ የተደበቀ ቁጣ ተቃዉሞዉን ባደባባይ ይዘርገፈዉ ገባ።

ካርተር የመካከለኛዉ ምሥራቅ «የሠላም ደሴት» ያሏት ጥንታዊት ሐገር በአመፅ፣ ሁከት፣ ግድያ ተተረማሰች።ኮሚንስቶች፣ዴሞክራቶች፣ብሔረተኞች፣ እስላማዉያን ባንድ አብረዉ የመሩት ሕዝብ የአሜሪካኖች ጥይት፣የአሜሪካ-እስራኤል-ብሪታንያ የስለላ መረብ፣ የአረቦች ገንዘብ አልበገረዉም።«ሞት ለሻሕ»ን ይፈክር ያዘ።

ሻሁ የዘመናት አንፀባሪቂ ጀንበራቸዉ በ38ኛዉ ዓመት ከምዕራብ አድማስ ጥግ መድረሷን የተረዱት መሠለ።ጥር 1979 «ለዕረፍት» በሚል ሰበብ ጓዛቸዉን ጠቅልለዉ ከቴሕራን ዉልቅ አሉ።በወሩ የአመፁ በተለይ እስልምናን እንደ ርዕዮተ ዓለም አንግበዉ የሚታገሉ ወገኖችን መጀመሪያ ኢራቅ ኋላ ፈረንሳይ ሆነዉ ይመሩና ያስተባብሩ የነበሩት ታላቁ አያቱላሕ ሩሆላሕ ኾሚኒ ከ16 ዘመን ስደት በኋላ ቴሕራን ገቡ።የካቲት 1 1979።

«ኢማሙ ገና ወደ ፈረንሳይ ከመሰደዳቸዉ ወይም አብዮቱ መልክና ቅርፅ ከመያዙ በፊት የሐገሪቱ መሪ መሆናቸዉ ሐቅ ነዉ።ምን ማለት ነዉ ሕዝብ እሳቸዉን ከተከተለ፣የሚሉትን ከሰማና ገቢር ካደረገ ወደድንም ጠላንም እሳቸዉ መሪ ናቸዉ።»

ከኮሚኒ ተከታዮች አንዱ።

በርግጥም የኢራን ሕዝብ እንደ

ታላቅ መሪ በደማቅ ስርዓት ተቀበላቸዉ።የሚሉትንም ገቢር ያደርግ ገባ።የሻሁን አገዛዝ ጥላቻ ብቻ ባንድ አብረዉ የነበሩት ኮሚንስቶች፣ዴሞክራቶችና ብሔረተኞች በእስላማዉኑ ተራ በተራ እየተደፈለቁ ተበታተኑ።ኾሚኑ ቴሕራን በገቡ በአስረኛዉ ቀን የኢራን አብዮት ድል በይፋ ታወጀ።የካቲት 1979።ዛሬ 40 ዓመቱ።

ከወር በኋላ በተደረገዉ ሕዝበ ዉሳኔ የአምስት ሺሕ ዘመን ባለታሪኳ፣የፋርሶች ስልጣኔ መሠረትዋ፣ የነዳጅ ዘይት ሐብታሚቱ ሐገር ከ2500 ዘመን በላይ የፀናባትን ንጉሳዊ አገዛዝ በይፋ አስወግዳ እስላማዊት ሪፐብሊክ ሆነች።የመካከለኛዉ ምሥራቅ የፖለቲካ አጥኚ ፕሮፌሰር ዓሊ አንሳሪ እንደሚሉት የኢራን አብዮት በጣሙን የመካከለኛዉ ምሥራቅን በመጠኑም የዓለም ፖለቲካዊ ሥርዓትን ለዉጦታል።

«እስላማዊዉ አብዮት በዓለም ላይ ያስከተለዉ ተፅዕኖ ከፍተኛ ነዉ።መካከለኛዉ ምሥራቅን ቀይሮታል።የዩናይትድ ስቴትስና የምዕራባዉያንን ቁልፍ ተባባሪ አስወግዷል።ከዚያ ጊዜ በኋላ የመካከለኛዉ ምሥራቅን እንቅስቃሴ በሙሉ እየነካ ነዉ።»

በርግጥም የአረብ-እስራኤል ጦርነት-ከአረብ እስራኤል ይልቅ የኢራን እስራኤል ጦርነት ዓይነት መልክ ይዟል።የሊባኖስ፣የሶሪያ፤የኢራቅ፣ የሳዑዲ አረቢያ የባሕሬን፣ አሁን ደግሞ የየመን ጦርነት፣ፖለቲካዊ ዉዝግብ፣የስልጣን ሽኩቻ ይሁን ሕዝባዊ አመፅ ባንድ ወይም በሌላ መልኩ የእራን እጅ አለበት።

ዩናይትድ ስቴትስ ለረጅም ጊዜ ጥቅሟ «አደገኛ» የምትለዉን አብዮት ለመቀልበስ ገና ከጅምሩ መሞክሯ አልቀረም።የቀድሞ ታማኟን መደገፍ ቀዳሚዉ ነበር።ይሁንና ሐገር አልባዉን ንጉስ አንዴ በሕክምና ሌላ ጊዜ በሰብአዊነት ሰበብ ከሆስፒታል-ሆቴል ስታመላልስ ከ1953ቱ መፈንቅለ መንግስት ጀምሮ አሜሪካ ላይ ያቄመዉ የኢራን ሕዝብ በተለይም ታሪኩን የሰማዉን ወጣት ለበቀል ከማነሳሳት በስተቀር ለዋሽንግተንም ለስደተኛዉ ንጉስም የተከረዉ የለም። 

ሕዳር 4 1979።አሜሪካ ላይ ያቄሙት የኢራን ወጣቶች በቴሕራን የዩናይትድ ስቴትስ ኤምባሲን ወረሩ።«በመስኮቴ በኩል ወደ ዉጪ ስመለከት የኾሚንን ፎቶ ግራፍ ያነገቡ ወጣቶች ኤምባሲዉ አጥር ላይ ሲንጠላጠሉ አየሁ።ያ ዕለት ለኔ በጣም አስፈሪ ቀን ነዉ።»

የያኔዉ የኤምባሲዉ ባልደረባ ባሪይ ሮዘን።ወጣቶቹ 52 አሜሪካዉያንን አገቱ።የአጋች-ታጋች አስለቃቂዎች ድራማ ከ444 ቀናት በኋላ አብቅቷል።ሁሉም ታጋቾች ተለቀዋል።መዘዙ ግን ዛሬም በአርባ-ዓመቱ ቴሕራንና ዋሽግተኖችን እንዳወዛገበ ነዉ።

የኢራን አብዮት ከፈነዳ ወዲሕ ዩናይትድ ስቴትስ 6 ፕሬዝደንት ቀያይራለች።የኢራንን እስላማዊ አብዮተኞች ለማጥፋት ያልዛተ ፕሬዝደንት የለም።የኢራን እስላማዊ አብዮተኞችም «ትልቋ ሰይጣን» የሚሏትን አሜሪካንን ያለወገዙ «ሞት ለአሜካን»ን ያልፈከሩ-ያላስፈከሩበት ጊዜ የለም።

ኢራን ድብቅ የኑክሌር መርሐ-ግብር እንዳለት ከታወቀ ወዲሕ ደግሞ የሁለቱ መንግስታት ዉዝግብ

መልኩን ቀይሮ ኑክሌር ቦምብ-የመስራት አለማስራት ባሕሪ ይዟል።ዉዝግቡን በድርድር ለመፍታት የሞከሩት፣ከአዉሮጳና ከቻይና ኃያላን መንግስታት ጋር ተባብረዉ ከኢራን ጋር የተስማሙት ፕሬዝደንት ባራክ ኦባማ ነበሩ።ኦባማ በትራምፕ ሲተኩ ግን የነበረዉ ሁሉ እንዳልነበር ሆነ።

«ዩናይትድ ስቴትስ ከኢራን ጋር የተደረገዉን ስምምነት ማፍረሷን ዛሬ አዉጃለሁ።ከጥቂት ጊዜ በኋላ በኢራን ላይ ተጥሎ የነበረዉን ማዕቀብ ዳግም የሚያፀና ፕሬዝደንታዊ ትዕዛዝ እፈርማለሁ።በጣም ከፍተኛ ደረጃ ያለዉን ምጣኔ ሐብታዊ ማዕቀብ ገቢር እናደርጋለን።»

ፕሬዝደንት ዶናልድ ትራምፕ ግንቦት 2018።ማዕቀቡም ዳግም ተጣለ።ዉግዘት፣ፉከራ፤ሽኩቻ፣ የእጅ አዙር ዉጊያዉም ከየመን-እስከ ፍልስጤም፣ ከሶሪያ እስከ ሊባኖስ ቀጠለ።

የቴሕራን መሪዎች እንደሚሉት በአሜሪካ-እስራኤሎች የሥለላ መረጃ፣ ከሶሪያ በስተቀር በአረቦች ገንዘብ የተደገፈዉን የኢራቅን ጦር ስምንት ዓመት ተዋግተዉ ድል አድርገዋል።ዩናይትድ ስቴትስ ኢራቅን ወርራ የባግዳድ ቤተ-መንግሥትን ለቴሕራን ወዳጆች ለማስረከብ ተገድዳለች።

የዩናይትድ ስቴትስ የቅርብ ወዳጅ ሳዑዲ አረቢያ የምትመራቸዉ የዓረብ መንግስታት በኢራን የሚደገፉ የየመን አማፂያን ለማጥፋት ያዘመቱት ጦር የመን ዉስጥ ይዳክራል።አራተኛ ዓመቱ።በኢራንና ሩሲያ የሚደገፉትን የሶሪያዉን ፕሬዝደንት በሽር አል-አሰድን ለማስወገድ ዩናይትድ ስቴትስ የምትመራቸዉ 29 መንግሥታት በቀጥታም፣በተዘዋዋሪም፣በዲፕላሚስም፣በገንዘብም፣ በጦርም መዋጋት ከጀመሩ-ስምንት አመታቸዉ። እስካሁን አሸናፊ ካለ በሽር አል-አሰድ ናቸዉ። አሜሪካ በትራምፕ ዘመን #Cripling የሚያሽመደምድ ያለችውን ማእቀብ ኢራን ላይ ጥላለች።

ህሩይ ወልደ ስላሴ

የዛሬው የታላላቅ ሰዎች ዝግጅታችን እውቁን የአማርኛ ስነጽሁፍ አባት ህሩይ ወልደ ስላሴን ይዘክራል፡፡

ባሕር ዳር፡ ህዳር 30 / 2009 ዓ.ም (አብመድ) ህሩይ ወ/ስላሴ ከአባታቸው አቶ ወልደ ስላሴ እና ከእናታቸው አመተ ማርያም ዜና ግንቦት 1 1871 ዓ ም የተወለዱ ሲሆን በአባታቸው በኩል መርሃ ቤቴ በእናታቸው ወገን ደግሞ መንዝ ናቸው ፡፡
የቤተክርስቲያን አስተዳዳሪ የሆኑት አባታቸው ልጃቸውን ለማስተማር ቆርጠው በመነሳታቸው ህሩይን በሰባት አመታቸው እንዲማሩ አቅራቢያቸው ወደሚገኝ ቤተክርስቲያን ላኳቸው ፡፡
በቀለም አያያዛቸው በመምህራቸው ደብተራ ስነ ጊዮርጊስ አድናቆትን ያተረፉት ህሩይ በሁለት አመት ውስጥ የግእዝ ትምህርትን አቀላጥፈው መናገር ሲችሉ የፊደል አጣጣልን ግን ዘግይተው ነው የተለማመዱት ፡፡

የህሩይን ምጡቅ ችሎታ የተረዱት አባታቸው የተሻለ ትምህርት እንዲማሩ እድሜያቸው አስር ዓመት ሲሆን መድሃኒ አለም ወደተባለ የአብነት ትምህርት ቤት በመላክ ለልጃቸው መማር ትልቁን ሚና ተጫውተዋል፡፡
በጊዜ ሂደትም ህሩይ ውዳሴ ማርያምን እና ሌሎችንም የቅዳሴ መጻህፍት በማጥናት የዲቁና እና የቅስና ማእረግን አግኝተዋል፡፡
ህሩይ በዕውቀት እንዲታነጹ ጉልህ እገዛ ያደረጉላቸው አባታቸው በ53 አመታቸው በሞት ሲለይዋቸው ህሩይ ገና የ13 አመት ታዳጊ ነበሩ ፡፡

ህሩይ በአባታቸው ሞት ቢደናገጡም ትምህርታቸውን በጀመሩበት ትምህርት ቤት አጠናክረው በመቀጠል ከቀለሙ ጎን ለጎን ወደእርሻው ፊታቸውን በማዞር የተዋጣላቸው አርሶአደር ሆኑ፡፡
በግብርናውም ዘርፍ ተጠቃሚ በመሆን ብዙ የቀንድ ከብት እና ፈረሶች ማርባት ችለዋል ፤ምንም እንኳ ጥሩ የፈረስ ጋላቢ ባይወጣቸውም ፡፡
የህሩይ የስነ ጽሁፍ ዕውቀት ከጊዜ ወደ ጊዜ እያደገ በመምጣቱ የሰላሌ አገረ ገዥ የደጃዝማች በሻህ የግል ጸሃፊ እስከ መሆን ደርሰዋል ፡፡
በጸሃፊነት ብዙም ሳይቆዩ የንጉስ ሃይለስላሴ አባት የራስ መኮንን ጸሃፊ ሆነው አገልግለዋል ፡፡
በኋላም ወደ ሸዋ - አድአ በርጋ በመጓዝ ለቀኝ አዝማች መቁረጭ በግብር መዝጋቢነት ተቀጥረው ሰርተዋል ፡፡
በዚህም ስፍራ ተወዳጅነት በማትረፋቸው ከአሰሪያቸው ‹ የሆነው ፍሬ ›የሚል ስያሜን አግኝተዋል ፡፡

ህሩይ ለአጭር ጊዜም ቢሆን ይህ ስማቸው በመግነኑ የተነሳ በርካታ መኳንንቶች ለማሰኮብለል ጥረት ቢያደርጉም ህሩይ ግን በቀላሉ የሚደለሉ አልሆኑም ፡፡
የቀኝ አዝማች መቁረጭ እና የህሩይ መለያየት ቁርጥ የሆነው የጣሊያንን ወረራ ለመመከት ዳግማዊ ዓጼ ምኒልክ በ1887 ዓ.ም የክተት አዋጅ ባሳወጁበት ወቅት ነው ፡፡
አዋጁን ተከትለው ቀኝ አዝማቹ ጠላትን ለመፋለም ወደጦር ግንባር በመዝመታቸው የስራ ግንኙነታቸው ተቋረጠ ፡፡
ህሩይ በጣሊያን ወረራ ወቅት ከጽህፈት ስራቸው በመነጠል ለተወሰነ ጊዜ በትውልድ ቀያቸው ቆይተዋል ፡፡

ከጦርነቱ በኋላ ህሩይ የመጽሃፍ ቅዱስ ጥናት በእንጦጦ ኪዳነምህርት አከናውነዋል ፡፡
የህሩይ የስነ ጽሁፍ ስራ እየናኘ በመምጣቱ የዳግማዊ ምኒልክ የግል ታሪክ ጸሃፊ የሆኑት ጸሃፌ ትዕዛዝ ገብረ ስላሴ አስጠርተዋቸው ከተወያዩ በኋላ አንድ ቁና እህል ወይም 5 ኪሎ ግራም እህል በወር እየተሰጣቸው ለመስራት ወሰኑ ፡፡

በሁለት አመት ቆይታቸው ህሩይ 27 ያህል መጽሃፍትን በማጥናት መተርጎም ችለዋል፡፡
ይህን እንዳጠናቀቀቁ ከዳግማዊ ምኒልክ አራት ያህል ሽልማቶችን ከአንድ የእጅ ሰአት ጋር ተሸልመዋል ፡፡
ህሩይ የተለያዩ የስነጽሁፍ መጻህፍትን እና ፍትሃ ነገስት የተባለውን ታሪካዊ መጽሃፍ አጥንተዋል ፡፡
ቤተሰብ ለመመስረት የተነሱት ህሩይ የጸሃፈ ትዕዛዝ ገብረስላሴን ልጅ እንዲያገቡ ቢታጭላቸውም በድህነታቸው ምክንያት ሳይሳካላቸው ቀርቷል፡፡
ይሁን እንጂ ሃሳባቸውን ለማሳካት ወደ ቀዬአቸው ደን አቦ በመመለስ ሚስት ሲያፈላልጉ ከቆዩ በኋላ ግንቦት 17 1895 ዓ.ም. ጎጆ ወጡ፡፡

ህሩይ ሚስታቸው ባተሌ የቤት እመቤት ከሚባሉት ተርታ በመሆናቸው ለስኬታቸው ቁልፍ ሆነዋል ፡፡
በ1882 ዓ ም. በኢትዮጵያ ድርቅ ተከስቶ በርካታ እንሰሳት በማለቃቸው ንጉስ ምኒልክ ከፈረንሳይ ሃገር የእንሰሳት ዶክተሮችን ለማስመጣት ወሰኑ ፡፡
ሆኖም ወደፈረንሳይ ተጉዞ ለመደራደር ብቃት ያላቸው ህሩይ መሆናቸውን ወልደ ጻድቅ የተባሉ የቤተመንግስት ሰው በመጠቆማቸው እንዲሰሩ ግዳጅ ተሰጥቷቸው ወደ ፈረንሳይ አቅንተዋል ፡፡
እዚያም የተሰጣቸውን አደራ በብቃት ለመወጣት ቡድኑን አስተባብረው ተልዕኳቸውን አሳክተዋል ፡፡
በ1890 ዓ.ም. ህሩይ ወርሃዊ ደመወዛቸው ወደ 10 ብር ከፍ ብሎላቸው የተጣለባቸውን የስራ ሃላፊነት በተሻለ መንገድ ወደ መስራት ተሸጋገሩ ፡፡

ቀጣዩን ክፍል ሳምንት እናቀርብላችኋለን

ለህብረተሰብ ለውጥ እንተጋለን!!
የአማራ ብዙሃን መገናኛ ድርጅት