Monday, September 24, 2018

china ethiopia debt trap policy

የቻይናና እዳ ውስጥ የመዝፈቅ ፖሊሲና የኢትዮጲያ ወዳጅነት ሲቃኝ
ፀሃፊው ስሜነህ ተረፈ
ጠቅላይ ሚር ዶር አብይ አህመድ በቻይና ጉብኝታቸው ወቅት ቻይና ለኢትዮፒያ የሰጠቻቸውን ብድሮችን ወለዱን እንድትቀንስና የመክፈያ ግዜው እንዲራዘም የቻይና የኤክዚም ባንክ ሃላፊ ሲነግሩ የቻይናው ፕሬዝዳንትም የባህር በር ለሌላቸው ትናንሽ ደሴቶች ለሆኑ የእፍሪካ ሃገራት ተወለድ ቅነሳ ወይም ስረዛ እንደምታደር ችን ፒንግ ፍንጭ ሰተዋል። ቻይና በአበዳሪነት ተቀባይነቱዋ እንዲቀንስ አትፈልግም። ዶር አብይም በብድር የተገኝ ገንዘብን ያባከነው ሜትልክ 1 ወር ውስጥ ለሁለት እንዲከፈል ትእዛዝ አስተላልፈዋል። ቻይና ያላትን ትርፍ ተቀማጭ ገንዘብ ስራ ላይ ማዋል ትፈልጋለች ለዚህ ድግሞ ወጣት ህዝብ ያላት አፍሪካ ምቹ ናት። ቻይና አገራዊ አጠቃላይ ምርቱዋ ከአሜሪካ አልፎ የሄደ ሲሆን የአለማችን ግዙፍ ምጣኔ ሃብት ባለቤት ሆናለች። ምንም እንኩዋን በሊበራል ሞክራሲ የምትመራ አገር ባትሆንምና ውስጣዊ ዲሞክራሲ ባይኖራትም በሃገሩዋ ስራ ያጣ ህዝቡዋን አዲስ የስራ ዘርፍ ለማስገኘት አፍሪካን በእጅጉ  ትፈልጋታለች የአፍሪካ ህዝብ 1ቢሊየን ሲሆን የቻይና ደግሞ 1.3 ቢሊየን ነው። ከዚህም።በላይ ቻይና
ከትራምፕ አሜሪካ ጋር በገባችው የንግድ ጦርነት የአፍሪካን ገበያንና ድጋፍን  ትሻለች ምንም እንኩዋን አሜሪካ እየተገለለች ብትመጣምና በአለም ያላት ተሰሚነት ማዘቅዘቅ ከጀመረ ቢሰነብትም፣ በአለም አቀፍ መድረኮች ቻይና የድርሻዋን እንዳትወጣ አሜሪካ እንቅፋት ሆናባታለች በዚህ ምክንያት እንደ አፍሪካ አህጉር አገራትን ድጋፍ ትሻለች ስለዚህ ብድሮቹዋ ላይ ብትለሳለስ አስገራሚ አይሆንም። ምእራባውያን በአፍሪካ አህጉር ከቻይና ጋር መወዳደር አልቻሉም በእፍሪካ የተፈጥሮ ሃብት ያላቸውን እንድ አንጎላ፤ ዛምቢያ ታንዛንያ እንዲሁም ሰፊና ለም መሬት ያላቸውንና ቁልፍ አቀማመጥ ያላትን ( strategic)  የሆነችውን እንደ ኢትዮፒያ ያሉ ቁልፍ አገራት ቻይና በእጅጉ ትፈልጋቸዋለች።
በቅርቡ የአፍሪካ ሃገራት ከቻይና ጋር ባደረጉት ስብሰባ የቻይናው ፕሬዝዳንት ዢንፒንግ ለአፍሪካ ሃገራት ተጨማሪ 60 ቢሊየን ዶላር ኢንቨስትመንትና ብድር ለመስጠት ቃል ገብተዋል ፡፡ /ሚር / አብይም ለሁሉም ብድሮች ባይሆንም ቻይና ለኢትዮጲያ የሰጠችውን ብድር ወለድ እንድትቀንስና የመክፈያ ግዜውን እንዳታራዝም ጠይቀው ተሳክቶላቸዋል ፡፡ የቻይናው መሪ ደሴት ለሆኑና የባህር በር ለሌላቸው የአፍሪካ ሃገራት የእዳ ቅነሳን እንደምታደርግ መናገራቸው እፎይታን ሰቷል፡፡ ከፍተኛ የእዳ ጫና ያለባት ሃገር የሆነችው ኢትዮጲያ ከሃያ አምስት ቢሊየን ዶላር እዳ ውስጥ ወደ አስር ቢሊየን የሚደርሰው ከቻይና የተወሰደ ብድር ነው፡፡
አፍሪካዊቷ ዛምቢያ የመብራት ሃይል ኩባንያዋንና፣ አየር ማረፊያዋን ለቻይና ለማስረከብ ተገዳለች ይህችው ሃገር የቻይና ከፍተኛ እዳ ቢኖርባትም መበደሯን ግን አላቆመችም ፡፡ ቻይና ለአፍሪካ የሰጠችው እዳ ቀላል የማይባል ከመሆኑም በላይ አንዳንድ ሃራት ሲሪላንካንና ጎረቤት ጅቡቲን ጨምሮ ትልቅ እሚባውን ሃገራዊ ሃብታውን ለቻይና ማስያዝ ጀምረዋል ፡፡ የቻይና ሃገራትን በእዳ ወጥመድ ውስጥ በመክተት የመተብተብ ዲፕሎማሲ (debt trap diplomacy) ብዙ ሃገራትን አጥምዶ ይዟል፡፡ ቻይና ምንግዜም ቢሆን ከየትኛውም ሃገር ያላትን ግንኙነት በረጅም ግዜ ተጠቃሚነቱዋ አስልታ የምትገባ ሲሆን እርሷ በቀላሉ ብድርን ለአፍሪካ ሃገራት በተለይም ሰብአዊ መብትን ለማያከብሩና የአምባገነንነት ዝንባሌ ላላቸው የአፍሪካ ሀገራት ቀላል የማይባል የእድሜ ማራዘሚያን የፈጠረ ቢሆንም ሃገራቱን ግን ለከባድ እዳ ዘፍቋል፡፡ ምእራባውያን እነኚህ ሃገራት የኢኮኖሚ ሪፎርምን እንዳያደርጉ የፋይናንስ ምንጭ ሆናለች ብለው ይከሷታል ቻይና ብድር ስትሰጥ የሰብአዊ መብት ሪኮርድን አታይም ይህን አድርግ ይህን ለውጥ ብላም መንግስታትን አትጫንም ነገር ግን የተፈጥሮ ሃብትን መቆጣጠርን ታስቀድማለች፡፡
ባለፉት ኢህአዴግ መራሽ ዘመን በየአመቱ ብቻ ከውጭ በብድርና እርዳታ 2እስከ 3 ቢሊየን ዶላር ድረስ ያኝ ነበረ። ይህ ገንዘብ ኢትዮጲያም ሆነች መሪዎቻችን አይተውት የማያውቁት ነው።  በዚህ  ከውጭ በመጣ ገንዘብ የኢኮኖሚ እድገቱ ተደግፎ ቆይቶአል። ነገር ግን ገዥው ፓርቲ ራሡን ወደ ገዥ መደብነት ( oligarcy ) በመቀየር በህዝብ ስም የመጣን ገንዘብ በሙስና ከመቀርጠፍ አንስቶ ወደ ውጭ ያሸሽ ገባ አገር አስተዳድራለሁ የሚለው መንግስት የአገርን ሃብትና ንብረትን በራሡ ቁጥጥር ስር በማዋል ሙስናና ዝርፊያው ቀጠለ፣ ህዝብ  ፍትህ ማግኘት አልቻለም የተለየ ሃሳብ ያነሱ የድርጅት አባላትን ሳይቀር ቆይ ጠብ እስር ቤት ትበሰብሳለህ ይባል ገባ። በዚህ የውጭ ገንዘብ የኢኮኖሚ እድገትን አስገኛለሁ ማለት በጉሉኮስ እየተሰጠው ሆስፒታል የሚኖር ሰው ማለት ነው ።ሙስናው በወጣቱ ዘንድ ቁጣን ያስነሳ ሲሆን እውቁ ግሪካዊው ፈላስፋ እንደሚለው <<በፖለቲካ ዓለም ውስጥ ከአማልክቶች በስተቀረ ማንም ተመልካች አይሆንም››  እንደሚለው  አብዛኛው  የሃገራችንን የፖለቲካ ቲያትር ተመልካች ተደርጎ የነበረውና ጥቂት የነባር አመራሮች በሚተውኑበት ቲያትር ውስጥ በፌስ ቡክ አማካይነት ተሳታፊ መሆን <span style="font-family:Nyal
...