Friday, March 29, 2019

ከንቱ ነው

‹‹ኒዕመቱ ዱኒያ በይነል ፈኺዘይን ››
(አሌክስ አብርሃም )

ብየሽ የነበረው ማግባት ምናባቱ
ብየሽ የነበረው ትዳር ማለት ከንቱ
ኡመቱ ለዱኒያ ሲሻኮት ሲለፋ
አለች ያልናት አለም ከጃችን ስጠፋ ….

አንድ ነገር ገባኝ ሹክ አለኝ መለይካው
በነብስህ እልፍኝ ውስጥ ከንቱ ነው ፍራንካው !
ከንቱ ነው ጭብጨባው
ከንቱ ነው ጉልበቱ
ከንቱ ነው ስልጣኑ
ከንቱ ነው ወረቱ !
እዛም እዛም አትጫር
ከንቱ ነው እሳቱ !
የመምጫ መሄጃው
ፍጥረተ ኡመቱ …..
አንድ ነገር ገባኝ
እኔ ያንች ገልቱ …..

ፍቅር በሌለበት ዱኒያ ማለት ጤዛ
አቅልን ስቶ መሮጥ መዋከብ ወ….ደዛ !
የምን መንጀላጀል የምን ነገ ዛሬ
ጥቅልል ከመሻትሽ ኒካየን አስሬ
ፍቅር አንችን ብቻ
ውድድድ አይንሽን
ፍቅር አፍንጫሽን
እብድ ለከንፈርሽ
መልመድ ከጠረንሽ
ለ…..ሽ ከደረተሸ
ጡትሽን መከዳ …
ኧረ እ……..ዳ !

ከዛ …..
እንደሰማይ መብረቅ
ካየር እንደጣሉት ጋን የሚያህል ፈንጅ




ተምዘግዝጌ …. የሳት ከተማሽ ውስጥ እልም ነው እንጅ !

የኔ የሰማይ መና ሃላል የነብስ ሃቄ
ቤቴን በፈገግታሽ ቤትሽን በሳቄ
‹‹ኒዕመቱ ዱኒያ በይነል ፈኺዘይን ››
በፍቅርሽ ሰክሬ በጆሮሽ የምለው
ለካስ ጀነት ያለው በሃቂቃ ሚስቴ ጭኖች መካከል ነው !!

Wednesday, March 13, 2019

የዘርአያቆብ ፍልስፍና ሃቲት

ፈላስፋው ዘርአያቆብ "እስራኤላውያን በእግዝአብሄር የተመረጡ ሕዝቦች ናቸው የሚለውን" የሙሴን መሠረታዊ አስተምህሮን አይስማማበትም ። መናፍቁ እና ጠርጣራው #Heretic Philosopher ፈላስፋው ዘርአያቆብ የሙሴን መሰረታዊ አስተምህሮቶችን ይጠራጠራል ።

ዘርአያቆብ እግዝአብሄር ለአህዛብ ሚስጥሩን መችልም አይገልጥላቸውም የሚለውን በሙሴ የተጻፈውን የመዝሙረ ዳዊትን ጥቅሥ አይስማማበትም ። ይሁን እንጂ ጸሀፊው የካቶሊክ ቄስ ከሆነ ለአይሁድ ባላቸው ጥላቻን ማንጸባረቁ ሊሆን ይችላል ።

በመዠመር ያዘርአያቆብ ማነው ? ትውልዱስ እንፍራንዜ (ጎንደሬ) ወይስ የአክሱሜ ? ወይስ የካቶሊክ ካህን ?  ። ይሄ መታወቅ አለበት። ማንነቱን ማወቅ አስፈላጊ የሆነበት ምክንያት ጸሐፊው ኢትዮጲያዊ ላይሆን ይችላል የሚል ጥርጣሬ ስላለ ነው። 

ፕሮፌሰር ጌታቸው በጻፉት መጽሀፍ እንፍራንዜ ሲያደርጉት ሌሎች በተረጎሙት ደግሞ በወቅቱ በነበረው በካቶሊኮችና ኦርቶዶክሶች የሃይማኖት ውዝግብ ከአክሱም በሃይማኖት ክፍፍል ምክንያት ሸሽቶ ወደ ጎንደር የተሰደደ ትግሬ ያደርጉታል ።
ዲያቆን ዳንኤል ክብረት ስለ ዘርአያቆ ትውልድ ስፍራ የትውልድ ስፍራ የራሱን ሃሳብ ሲገልጽ ፦

" የዘርአ ያእቆብ የዓለም ስሙ ‹ወርቄ› ነው፡፡ ‹ወርቄ፣ ብርቄ፣ ድንቄ› የሚሉ የስም አወጣጦች በአማራው አካባቢ እንጂ በአኩስም አካባቢ የተለመዱ ስሞች አይደሉም፡፡ ኡርቢኖ በደብረ ታቦር አካባቢ ሲኖር የሰማውን ስም መሆን አለበት የተጠቀመው፡፡" ይላል በዳንኤል ክብረት እይታ ዘርአያቆብ የጎንደሬ ስም ነው የተጠቀመው ።

ዲያቆን ዳንኤል ሲጠቅሥ " እንዲያውም ‹እንደዚህ ከሀገር ወደ ሀገር ስሄድ ወደ አኩስም እመለስ ዘንደ አልፈቀድኩም፤ የካህኖቿን ክፋት ዐውቅ ነበርና›(ያሬድ፣25) ይላል፡፡ በዲያቆን ዳንኤል ክብረት እይታ "ዘርአ ያእቆብ በምንም መልኩ አኩስማዊ አይደለም ፡፡ አክሱምን በዚህ መጠን የሚጠላ አኩስማዊም ሊኖር አይችልም፡ በምክንያት የሚያምን ሰው ለዚህ ጥላቻው በቂ ምክንያት አላቀረበም፡፡ ዋና ማዕከላቸውን በአድዋ አድርገው ለነበሩት ካቶሊካውያን አኩስማውያን ቦታ ሊሰጧቸው አልፈቀዱም ነበር፡፡ የካቶሊክ ሚስዮናውያን መሠረት ሊጥሉ የፈለጉት በአኩስም ነበር፡፡ነገር ግን የአኩስም ካህናት አልፈቀዱም፡፡ይህንን ጥላቻ ነው ኡርቢኖ ያንጸባረቀው፡፡" ይላል።

ሌላው አብዛኛው ዘርአያቆብ እሚጠቅሳቸው ጥቅሦች ከመዝሙረ ዳዊት የተወሰዱ መሆናቸው ሌሎቹን የመጽሀፍ ቅዱስ ክፍሎችን በጥልቀት ያውቃል ወይ ሊያስብል ይችላል።

ዘርአ ያእቆብ ሙሴን ሲወቅስ ‹ወሙሴሰ ይቤ ኩሉ ሩካቤ ርኩስ ውእቱ - ሙሴም ሩካቤ ሁሉ ርኩስ ነው አለ› ይላል(215,9a)፡፡ ነቢዩ ሙሴ ራሱ በጋብቻ ጸንቶ የኖረ ነቢይ ነው፡፡ በምን መልኩ ይህንን ሊል አይችልም፡፡ ሙሴ ይህንን ነገር ለመናገሩ መጽሐፋዊም ትውፊታዊም ማስረጃ የለም፡፡ ዘርአ ያዕቆብ ዳዊት ከማወቅ (እርሱንም ሲደበቅ ደጋግሞ በማንበቡ)፣ ሐዲስን ከማንበብ የዘለለ የብሉይ ትምህርት የለውም ይላል ዲያቆን ዳንኤል ክብረት፡፡

ከሙሴ ይልቅ ግን ሐዋርያው ጳውሎስን በዚህ ጉዳይ ቢጠቅሥ ይመረጥ ነበረ ልምን ቢባል ጳውሎስ ከቻላችሁ እንደኔ አታግቡ ማለቱ በመልእክቶቹ የሚታወቅ ሲሆን ሐዋርያውም ራሱ ግን በዚህ ሊወቀስ የሚችል አይደለም ይህን ያለው ራሳቸውን በቅድስና ለሚለዩቱ ቅዱሳን ነው ፥ ምክንያቱም እርሱም ቢሆንም ግን የጋብቻን ክቡርነትንና የትውልድ መቀጠልን ነው ያስተማረው። ጌታ እየሱስም ጭምር "አንድ ሴት ለአንድ ወንድ" ብሎ ነው ያስተማረው። ጋብቻ ከሌለ ትውልድ ሊቀጥል እንደማይችል በጥንት ዘመንም የሚታወቅ ቀላል እውነት መሆኑ ይታወቃል ። ስለዚህ ዘርአያቆብ የቱ ቦታ ላይ ነው ሙሴ ሩካቤ ሁሉ እርኩስ እንዳለ ምንጩን አይጠቅሥም። በሙሴ ግዜ እንደውም እስራኤላውያን ህዝቡም ሆነ ነገስታቱ በርካታ ሚስቶችን ያገቡ ነበረ። ሙሴ ለነገስታቶች በሰጠው ምክር "ንጉሡ ሚስቶችን አያብዛ " የሚል ነው። በሃዲስ ኪዳን በአንድ ስለመወሰን ከመደንገጉ በስተቀር በብሉይ ዘመን ከአንድ በላይ ሚስት ማግባት እንደሚቻል ከብሉይ መጽፍሐት መረዳት ይቻላል ። በሙሴ ህግ የሚመሩት የእስራኤል ነገስታት ከአንድ በላይ ሚስቶችን አግብተው በርካታ ልጆችን እንደወለዱ መጽሐፈ ነገስት ያትታል ። ለምሳሌ።ንጉስ ዳትዊንስ የንጉስ ሰለሞን ልጅ ኢዮርብአም በርካታ ሚስቶች እንደነበሩዋቸው ማንበብ ይቻላል ።

ዘርአያቆብ መዝሙረ ዳዊት ላይ ብቻ ትኩረትን ስላደረገ ከብሔረ ኦሪት አሟልቶ መጥቀስ አልቻለም፡፡ የካቶሊክ ሚስዮናውያን ወደ ኢትዮጵያ ሲመጡ ቤተ ክርስቲያኒቱን የከሰሱበት አንዱ ክስ ‹ኦሪታዊት ናት› የሚል ነው፡፡ ለእነርሱ በንጉሥ ገላውዴዎስ ዘመን የነበሩት ሊቃውንት መልስ ሰጥተዋቸዋል፡፡ ዘርአ ያእቆብ የእነርሱ ወገን ካልሆነ በቀር ሙሴን በዚህ መልኩ አይጠቅሰውም፡፡ ዲያቆን ዳንኤል ክብረት ዘርአያቂብ ማለት ኡርቢኖ የተባለ የካቶሊክ መነኩሴ ነው።

ሌላው ዘርአያቆብ ስለ ንጉሥ ፋሲለደስ ያለው አመለካከት ነው ። "በዐመሉና በደም ማፍሰስ ጸና፣በጎ ላደረጉለት፣ ቤተ መንግሥትንና ያማሩ ቤቶችን ለሠሩለት፣ በጥበብ ነገር ሁሉም መንግሥቱን ላሣመሩለት ፈረንጆችን ጠላቸው› ይላል " ፋሲለደስ ቤቶችን ይወርስ ነበረ ሴቶችን አብሮአቸው ካደረ በሁዋላ ይገድላቸው ነበረ ሲል ንጉስ ፋሲልን ግፈኛ አድርጎ ያቀርበዋል።

በራሱ አንደበት እንዲህ ይላል " ፋሲለደስ ክፉን ነገር የሚሠራ ሆነ፡፡ ሰዎችን ያለ ፍርድ ይገድል ነበር፡፡ አመንዝራነትም ያበዛ ነበር፡፡ ሴቶችንም ከእነርሱ ጋር ካመነዘረ በኋላ ይገድላቸው ነበር፡፡ ዐመጻን የሚያደርጉ ሠራዊትንም ልኮ የድኾችን ሀገሮችና ቤቶች እንዲቀሙ ያደርግ ነበር፡፡

እግዚአብሔር ለክፉዎች ሕዝቦች ክፉውን ንጉሥ ሰጥቷቸው ነበርና፡፡ ስለ ንጉሡና ስለ ሕዝቡም ኃጢአት ረሀብና መቅሰፍት መጣ፡፡ ከረሃብ በኋላም ቸነፈር ሆነ፡፡ ብዙዎችም ሞቱ፡፡ ሌሎችም ፈሩ፡፡" ዘርአያቆብ በወቅቱ ለነበረው ማህበረሰብ በጎ አመለካከት አልነበረውም የህዝቡ ክፋት ፋሲለደስ የተባለ ክፉ ንጉስ እንደሰጣቸው አፍርጎ ነው የተረዳው።

ይሁንና ግን ፋሲለደስ በአጼ ሱስንዮስ ዘመን የነበረውን የሃይማኖት ውዝግብን ያስቆመና ፤ግራኝ አህመድን ወረራ ለመመከት መጥተው ነገር ግን ከግራኝ ሽንፈት በሁዋላ የኦርቶዶክስ እምነትን ወደ ካቶሊክ ለመለወጥ የሞከሩትን ፖርቱጋሎችን ያስወጣ ነው።

china port

Marine Gen. Thomas Waldhauser, the top U.S. military officer for Africa, told a congressional hearing last year that the U.S. military could face significant consequences if China took the port in Djibouti.

Tuesday, March 12, 2019

ከተማና ድንኩዋን የትም ይተከላል

ህንድ፥ ግብጽ፥ ሳኡዲ ፥እንዲሁም ቻይና አዳዲስ ከተሞችን እየገነቡ ይገኛሉ ። ሳኡዲ ከአፍሪካ ጋር በድልድይ የሚገናኝ ቀይ ባህር ጠረፍ ላይ ከጆርዳንና ግብጽ ቅርበት ባለው ስፍራ ግዙፍ ከተማን እየገነባች ነው።

ቻይና እየገነባች ያለችው ከተማ የ #USA ውን ኒው ዮርክ ሲቲን በግዝፈት የሚያስንቅ ሲሆን ከሆንግ ኮንግ ጋር በትላልቅ ድልድዮች እያገናኘችው ነው።

ጎረቤት ኬንያ እንኩዋን 6 የተለያዩ ግልጋሎት እሚውሉ ከተሞችን ልትገነባ ነው።  ለስፖርት ፥ ለቴክኖሎጂ ፥ ለህክምና ፥ ለመዝናኛ ...ወዘተ እሚውሉ ሲሆን በርካታ የዓለማችን ሀገርስት አዳዲስ ከተሞችን ከስክራች #Scratch እየገነቡ ይገኛሉ። ህንድ 12 አዳዲስ ትላልቅ ከተሞችን እየገነባች ትገኛለች ። ቻይናም ኒው ዮርክ ሲቲን እሚያስንቅ ከሆንግ ኮንግ ጋር እሚገናኝ ግዙፍ ከተማን እየገነባች ትገኛለች ።

እንዲሁም ቱጃሩ ቢል ጌትስ በአሪዞና በረሐ ውስጥ የቴክኖሎጂ የዘመነ ከተማን እያስገነባ ነው። ይህ ከተማ ያለ ሹፌር እሚነዱ መኪኖችን በአውራ ጎዳናዎቹ ላይ ይሽከረከራሉ። ይህ ከተማ ተሰርቶ ሲያልቅ 182 ሺህ ህዝብ መኖርያ ይሆናል ተብሎ ይጠበቃል .።

አሁን በአለም ዙሪያ እየተቆረቆሩ ያሉ ከተሞች በብዙ ነገራቸው ዘመናዊና የተራቀቁ ናቸው።

እኛ ግን አዲስ ከመፍጠር ይልቅ፥ የተፈጠረው ላይ ስለምናተኩር ነው እንጂ "ከተማ እና ድንኩዋን የትም ይተከላል" የሚለው ይትበሀል ረስተናል።

Monday, March 4, 2019

የዘርአያቆብ ፍልስፍና ሃቲት

ፈላስፋው ዘርአያቆብ "እስራኤላውያን በእግዝአብሄር የተመረጡ ሕዝቦች ናቸው የሚለውን" የሙሴን መሠረታዊ አስተምህሮን አይስማማበትም ። መናፍቁ እና ጠርጣራው #Heretic Philosopher ፈላስፋው ዘርአያቆብ የሙሴን መሰረታዊ አስተምህሮቶችን ይጠራጠራል ።

ዘርአያቆብ እግዝአብሄር ለአህዛብ ሚስጥሩን መችልም አይገልጥላቸውም የሚለውን በሙሴ የተጻፈውን የመዝሙረ ዳዊትን ጥቅሥ አይስማማበትም ። ይሁን እንጂ ጸሀፊው የካቶሊክ ቄስ ከሆነ ለአይሁድ ባላቸው ጥላቻን ማንጸባረቁ ሊሆን ይችላል ።

በመዠመር ያዘርአያቆብ ማነው ? ትውልዱስ እንፍራንዜ (ጎንደሬ) ወይስ የአክሱሜ ? ወይስ የካቶሊክ ካህን ?  ። ይሄ መታወቅ አለበት። ማንነቱን ማወቅ አስፈላጊ የሆነበት ምክንያት ጸሐፊው ኢትዮጲያዊ ላይሆን ይችላል የሚል ጥርጣሬ ስላለ ነው። 

ፕሮፌሰር ጌታቸው በጻፉት መጽሀፍ እንፍራንዜ ሲያደርጉት ሌሎች በተረጎሙት ደግሞ በወቅቱ በነበረው በካቶሊኮችና ኦርቶዶክሶች የሃይማኖት ውዝግብ ከአክሱም በሃይማኖት ክፍፍል ምክንያት ሸሽቶ ወደ ጎንደር የተሰደደ ትግሬ ያደርጉታል ።
ዲያቆን ዳንኤል ክብረት ስለ ዘርአያቆ ትውልድ ስፍራ የትውልድ ስፍራ የራሱን ሃሳብ ሲገልጽ ፦

" የዘርአ ያእቆብ የዓለም ስሙ ‹ወርቄ› ነው፡፡ ‹ወርቄ፣ ብርቄ፣ ድንቄ› የሚሉ የስም አወጣጦች በአማራው አካባቢ እንጂ በአኩስም አካባቢ የተለመዱ ስሞች አይደሉም፡፡ ኡርቢኖ በደብረ ታቦር አካባቢ ሲኖር የሰማውን ስም መሆን አለበት የተጠቀመው፡፡" ይላል በዳንኤል ክብረት እይታ ዘርአያቆብ የጎንደሬ ስም ነው የተጠቀመው ።

ዲያቆን ዳንኤል ሲጠቅሥ " እንዲያውም ‹እንደዚህ ከሀገር ወደ ሀገር ስሄድ ወደ አኩስም እመለስ ዘንደ አልፈቀድኩም፤ የካህኖቿን ክፋት ዐውቅ ነበርና›(ያሬድ፣25) ይላል፡፡ በዲያቆን ዳንኤል ክብረት እይታ "ዘርአ ያእቆብ በምንም መልኩ አኩስማዊ አይደለም ፡፡ አክሱምን በዚህ መጠን የሚጠላ አኩስማዊም ሊኖር አይችልም፡ በምክንያት የሚያምን ሰው ለዚህ ጥላቻው በቂ ምክንያት አላቀረበም፡፡ ዋና ማዕከላቸውን በአድዋ አድርገው ለነበሩት ካቶሊካውያን አኩስማውያን ቦታ ሊሰጧቸው አልፈቀዱም ነበር፡፡ የካቶሊክ ሚስዮናውያን መሠረት ሊጥሉ የፈለጉት በአኩስም ነበር፡፡ነገር ግን የአኩስም ካህናት አልፈቀዱም፡፡ይህንን ጥላቻ ነው ኡርቢኖ ያንጸባረቀው፡፡" ይላል።

ሌላው አብዛኛው ዘርአያቆብ እሚጠቅሳቸው ጥቅሦች ከመዝሙረ ዳዊት የተወሰዱ መሆናቸው ሌሎቹን የመጽሀፍ ቅዱስ ክፍሎችን በጥልቀት ያውቃል ወይ ሊያስብል ይችላል።

ዘርአ ያእቆብ ሙሴን ሲወቅስ ‹ወሙሴሰ ይቤ ኩሉ ሩካቤ ርኩስ ውእቱ - ሙሴም ሩካቤ ሁሉ ርኩስ ነው አለ› ይላል(215,9a)፡፡ ነቢዩ ሙሴ ራሱ በጋብቻ ጸንቶ የኖረ ነቢይ ነው፡፡ በምን መልኩ ይህንን ሊል አይችልም፡፡ ሙሴ ይህንን ነገር ለመናገሩ መጽሐፋዊም ትውፊታዊም ማስረጃ የለም፡፡ ዘርአ ያዕቆብ ዳዊት ከማወቅ (እርሱንም ሲደበቅ ደጋግሞ በማንበቡ)፣ ሐዲስን ከማንበብ የዘለለ የብሉይ ትምህርት የለውም ይላል ዲያቆን ዳንኤል ክብረት፡፡

ከሙሴ ይልቅ ግን ሐዋርያው ጳውሎስን በዚህ ጉዳይ ቢጠቅሥ ይመረጥ ነበረ ልምን ቢባል ጳውሎስ ከቻላችሁ እንደኔ አታግቡ ማለቱ በመልእክቶቹ የሚታወቅ ሲሆን ሐዋርያውም ራሱ ግን በዚህ ሊወቀስ የሚችል አይደለም ይህን ያለው ራሳቸውን በቅድስና ለሚለዩቱ ቅዱሳን ነው ፥ ምክንያቱም እርሱም ቢሆንም ግን የጋብቻን ክቡርነትንና የትውልድ መቀጠልን ነው ያስተማረው። ጌታ እየሱስም ጭምር "አንድ ሴት ለአንድ ወንድ" ብሎ ነው ያስተማረው። ጋብቻ ከሌለ ትውልድ ሊቀጥል እንደማይችል በጥንት ዘመንም የሚታወቅ ቀላል እውነት መሆኑ ይታወቃል ። ስለዚህ ዘርአያቆብ የቱ ቦታ ላይ ነው ሙሴ ሩካቤ ሁሉ እርኩስ እንዳለ ምንጩን አይጠቅሥም። በሙሴ ግዜ እንደውም እስራኤላውያን ህዝቡም ሆነ ነገስታቱ በርካታ ሚስቶችን ያገቡ ነበረ። ሙሴ ለነገስታቶች በሰጠው ምክር "ንጉሡ ሚስቶችን አያብዛ " የሚል ነው። በሃዲስ ኪዳን በአንድ ስለመወሰን ከመደንገጉ በስተቀር በብሉይ ዘመን ከአንድ በላይ ሚስት ማግባት እንደሚቻል ከብሉይ መጽፍሐት መረዳት ይቻላል ። በሙሴ ህግ የሚመሩት የእስራኤል ነገስታት ከአንድ በላይ ሚስቶችን አግብተው በርካታ ልጆችን እንደወለዱ መጽሐፈ ነገስት ያትታል ። ለምሳሌ።ንጉስ ዳትዊንስ የንጉስ ሰለሞን ልጅ ኢዮርብአም በርካታ ሚስቶች እንደነበሩዋቸው ማንበብ ይቻላል ።

ዘርአያቆብ መዝሙረ ዳዊት ላይ ብቻ ትኩረትን ስላደረገ ከብሔረ ኦሪት አሟልቶ መጥቀስ አልቻለም፡፡ የካቶሊክ ሚስዮናውያን ወደ ኢትዮጵያ ሲመጡ ቤተ ክርስቲያኒቱን የከሰሱበት አንዱ ክስ ‹ኦሪታዊት ናት› የሚል ነው፡፡ ለእነርሱ በንጉሥ ገላውዴዎስ ዘመን የነበሩት ሊቃውንት መልስ ሰጥተዋቸዋል፡፡ ዘርአ ያእቆብ የእነርሱ ወገን ካልሆነ በቀር ሙሴን በዚህ መልኩ አይጠቅሰውም፡፡ ዲያቆን ዳንኤል ክብረት ዘርአያቂብ ማለት ኡርቢኖ የተባለ የካቶሊክ መነኩሴ ነው።

ሌላው ዘርአያቆብ ስለ ንጉሥ ፋሲለደስ ያለው አመለካከት ነው ። "በዐመሉና በደም ማፍሰስ ጸና፣በጎ ላደረጉለት፣ ቤተ መንግሥትንና ያማሩ ቤቶችን ለሠሩለት፣ በጥበብ ነገር ሁሉም መንግሥቱን ላሣመሩለት ፈረንጆችን ጠላቸው› ይላል " ፋሲለደስ ቤቶችን ይወርስ ነበረ ሴቶችን አብሮአቸው ካደረ በሁዋላ ይገድላቸው ነበረ ሲል ንጉስ ፋሲልን ግፈኛ አድርጎ ያቀርበዋል።

በራሱ አንደበት እንዲህ ይላል " ፋሲለደስ ክፉን ነገር የሚሠራ ሆነ፡፡ ሰዎችን ያለ ፍርድ ይገድል ነበር፡፡ አመንዝራነትም ያበዛ ነበር፡፡ ሴቶችንም ከእነርሱ ጋር ካመነዘረ በኋላ ይገድላቸው ነበር፡፡ ዐመጻን የሚያደርጉ ሠራዊትንም ልኮ የድኾችን ሀገሮችና ቤቶች እንዲቀሙ ያደርግ ነበር፡፡

እግዚአብሔር ለክፉዎች ሕዝቦች ክፉውን ንጉሥ ሰጥቷቸው ነበርና፡፡ ስለ ንጉሡና ስለ ሕዝቡም ኃጢአት ረሀብና መቅሰፍት መጣ፡፡ ከረሃብ በኋላም ቸነፈር ሆነ፡፡ ብዙዎችም ሞቱ፡፡ ሌሎችም ፈሩ፡፡" ዘርአያቆብ በወቅቱ ለነበረው ማህበረሰብ በጎ አመለካከት አልነበረውም የህዝቡ ክፋት ፋሲለደስ የተባለ ክፉ ንጉስ እንደሰጣቸው አፍርጎ ነው የተረዳው።

ይሁንና ግን ፋሲለደስ በአጼ ሱስንዮስ ዘመን የነበረውን የሃይማኖት ውዝግብን ያስቆመና ፤ግራኝ አህመድን ወረራ ለመመከት መጥተው ነገር ግን ከግራኝ ሽንፈት በሁዋላ የኦርቶዶክስ እምነትን ወደ ካቶሊክ ለመለወጥ የሞከሩትን ፖርቱጋሎችን ያስወጣ ነው።

Ethiopia Debt Sustainability

የገንዘብ ስርአት ቁጥጥር ሊደረግበት ይገባል። ከለውጡ በፊት በኢትዮፒያ በኢትዮፒያ ልማት ባንክ በኩል ብድር ቢመቻችም ብድሩ ሳይመለስ #npl ማለትም #የማይመለሱ ብድሮች ይፋዊ በሆነው መረጃ #Non_Performing_Loans #NPL ወደ 40 በመቶ ከፍ ቢልም እስከ 70 በመቶ ይደርሳል በዘርፉ ባለሙያዎች ግምት።ለዚህ ምሳሌ እሚሆነው #Aika_Addis የተባለው የ#ቱርክ #ኩባንያ #አይካ_አዲስ በ8 ቢሊየን እዳ እሳቅፈው ሲሄዱ 29 ሚሊየን ዶላር ማሽን ቢያመጣም 150 ሚሊየን ዶላር እንዳመጣ ተደርጎ ብድር ከልማት ባንክ ተለቆለታል ። ይህም።ልማት ባንኩን አክስሮአል ።
አሁን ግን በዚህ አይነት መንገድ በተለይም ግብርና ዘርፍ እንሰማራለን ብለው ከልማት ባንክ ብድር ወስደው ያልከፈሉ በህግ እንደሚጠየቁ የብሄራዊ ባንክ ገዢ ጠቁመዋል ።

#small & medium eneterprisrs አነስተኛና መካከለኛ ተቁዋማት አበዳሪ
ያጡት በዚህ ምክንያት ነው ።
እሚያበድራቸው የለም ፥ ወጣቱ ስራ ያጣው በዚህ ምክንያት ነው።
አሁን ያለው ለውጥ መደገፍ የምንችለው በኢኮኖሚ ስልት ነው ስራ እድል ለወጣቱ መፈጠር እና ኤክስፖርት #import_Export_Trade #ወጪና_ገቢ_ንግድ መንቀሳቀስ አለበት ፥ ለዚህ ደግሞ መንግስት #ፕላን ማውጣት አለበት። የሀገሪቱ የውጭ ብድርን ጫና የመሸከም አቅም #Debt Sustainability መፈተሽ አለበት።  ከአቅም በላይ ብድርና ክፍያ የውጭ ምንዛሪውን ጠራርጎ እየወሰደው ነው። ሃገሪቱ ብድር ለመክፈል አጠራጣሪ ሁኔታ ውስጥ ልትገባ እንደነበረ ወይም #Default ልታደርግ እንደነበረ የብሄራዊ ባንክ ገዥ ዶ/ር ይናገር ደሴ ጠቆም አድርገዋል በቅርቡ በሰጡት ቃለ ምልልስ።

Sunday, March 3, 2019

Zar’a Ya’aqob Ethiopian philosopher

Zar’a Ya’aqob is not Ethiopian or there was no such philosopher called Zar’a Ya’aqob. The one known as Zara Ya’aqob was a pseudonym used by a 19th Century Freemason European — who penned the treatises as better known as the Hatetas.