Showing posts with label dr. Abey Ahmed. Show all posts
Showing posts with label dr. Abey Ahmed. Show all posts

Thursday, November 15, 2018

የሜቴክ ሙዝና ዝርዝር ፦

ተርባይን ለመግጠም የተዋዋለው ሜቴክ የህዳሴው ግድብ ተርባይን 16 ተርባይኖች ሲሆኑ አንዱ 6 ሚሊየን ዩሮ ሲሆን ያንዱ ዋጋ ነገር ግን ኦሪጅናል አልተገዛም የተገጠሙት ተርባይኖችም በትክክል መስራት አልቻሉም።

የስኩዋር ኮርፖሬሽን ፓወር ፕላስ ነው። ይህ ደግሞ በ10 ፕርሰንት ኮሚሽን የተበላበት ነው። ሌላው ያዩ ማዳበርያ ፋብሪካ መጀመርያ ላይ አዋጭ አልነበረም ግን አዋጭ እንደተደረገ ተደርጎ ኮሚሽን ተበልቶበት በሀሰት ሪፖርት ተዘጋጅቶ ሲሆን ፕሮጅክቱ በጀት ተያዘለት ከ5 ቢሊየን ብር ብላይ ነው ። ሲቪል ስራው ያለጨረታ ለተክልብርልሃን አምባየ የተሰጠ ነው።
ለመርክብ አላግባብ 300 ሚሊየን ወጭ የተደረገበት ነው።  ሁለት የንግድ መርከቦች ግዥ ነው። ሜቴክ መርከብ ያስፈልገኛል ብሎ ተፈቅዶለት የገዛው ሲሆን ። መርከቦቹ ግን  ለscrap ነው የተሽጡት። ምንም ስራ ላይ ሳይውሉ አሮጌ ሞዴል ናቸው ምንም አገልግሎት ሳይሰጡ ነው የተሸጡት።
ሌላው ኮሚሽን የተበላበት የታንኮች ግዥ ነው።  የመከላከያ ግዥ ሃልፊ የነበረው የሳሞራ ጉዋደኛ ነው አገናኝ ደላላው ።ታንኮቹ የተከፈለው ካዲስ ታንክ ዋጋ ጋር ተቀራራቢ ነው። በስፔር ፓርት እጥረት እየቆሙ ሄዱ። አዲስ መግዛት ሲገባ አዲስ ባለመግዛት ክፍተኛ ኮሚሽን ወስደዋል። 
የመከላከያ ፋውንዴሽን የሰራዊቱን አልባሳት ያስመጣል። ከጦር ምርሳርያ ግዥ ክምስራቅ አውሮፓ የሚገዙ የጦር መሳርያዎች ሲሆኑ የጅነራል ክንፈ ውንድም ነው ደላላው።
ኢትዮ ቴሌኮም የቻይና ኩባንያዎች የሃገሪቱ የመረጃ አርክይቭ software ሰርቨር ይህ ሶፍትውሩ ወደ መቀሌ ተወስዳል።
ይህ የቁልፍ  የግንዘብ ሚ/ር የምክላከያ ወዘተ የሃገሪቱ ቁልፍ ተቁዋማት መረጃ የያዘ ከ83 ኣ.ም. ጀምሮ መረጃን የያዘ ነው። 
የተወሰዱ በርካታ ብድሮች ስላሉ የእንዚህን ብድሮች መረጃን ለማጥፋት ሊሆን ይችላል። 
የደህነት ፥ የመከላከያ የገንዝብ ሚ/ር ወዘተ መረጃዎችን ይዞአል ይህ ሰርቨር።
የትራንስፖርት ጅቡቲ ያሉ የትራንስፖርት ማህበርስትን ያገለለ ነው። ግን ይህ የትራንስፖርት አገልግሎት ሰጪዎች ተገልለዋል የሜቴክንም የስኩዋር ኮርፖሬሽንም የሚይጉዋጉዙ ናቸው ለታጋይ ማህበራት ሲሰጥ የታግይ ምህበራትም ቢሆኑ በእኩል አልታዩም።
በዚህ ትራንስፖርት አገልግሎት 1.5 ቢሊየን ብር የተከፈለበት ነው። 

በወቅቱ በጅቡቲ አምባሳደር የነበረውሱሌይምስን ደደፎ ሜቴክንና መከላከያን አትተባበርም ተብሎ ስሙን ማጥፋት ጀመሩ የጅቡቲ ኤምባሲ አታሼ። ይህን አድሎአዊ አሰራርን ሲቃወም። አምባሳደር ሱሌይማን ለመርክቦቹ ማቆሚያ በውጭ ምንዛሬ አለግባብ ኪራይ መከፈሉን ሲቃወም ድብዳቤም ፅፎአል ለበላይ ሃላፊዎች።

16 ቤቶች ሜቴክ ገዝቶአል ኢምፔሪያልንና ፥ ሪቬራ ሆቴልን ብቻ መቶ ሚሊየን ብር ነው የተገዛው ። የሰው ኣልባ ኣውሮፕላን ቦዲና ድሮን እስራልሁ ቢልም ክመሬት መነሳት አልቻለም።

ለመከላከያ ስፔር ፓርቶች  ባግባብ አይገዛም። 
መክላክያ ታንክ ሲገዛ ራሱ ነው እሚገዛው መከላከያ ውስጥ የራሱ ግዥ ክፍል ቢኖረውም። በሰራዊቱ ግዳጅ አፈጻጸም እንቅፋት ሆነ ከጥራት በታች በተገዛ ታንክ ምክንያት።

በሜቴክ እማካይነት ሳሞራ ችይና ህንጻ አለው ። ብዚህ ወሬ አውርተሃል በሚል የታገዲም የታሰሩም አሉ አቶ ሲራጅ ነበረ የሜቴክ ቦርድ ሰብሳቢ። ያገሪቱ ሃብት በሜቴክ መዘረፉና በኢፈርት እጅ መያዙ ለዶ/ር አብይ መንግስት ፈተና ነው። 

Sunday, November 11, 2018

ምነው PM ትእግስት በዛሳ ?

ምነው ያብይ ትግስ በዛ ? የሚሉ አሉ ፦

ነገር ግን ከታሪክ ያለው ልምድ አንድ ግዜ ደም መፍሰስ ከጀመረ ወደሁዋላ መመለስ አይቻልም።
ስዚህ እያረጋጉ መቀጠሉ አማራጭ የለውም። መጭው ምርጫ የዚህችን አገር ህልውና ይወስናል በትክክል ከተደረገ እና  ህዝቡ የኔ የሙላቸውን መሪዎቹን ያለማንም ጣልቃ ገብነት ከተመረጠ መጭው ያገሪቱ እድል የቀና ይሆናል። ለምሳሌ ከሰሞኑ የተሰጠው የሚስትሮች ሹመት ብዙ ሲያንገርስግር ከርሞአል። ጠ/ሚሩ ወጭ እሚቀንስ ነው ፥ አስራሮችን ወዳእንድ እሚሰበስብ ነው ቢሉም ፥ የሚትሮችን ቁጥር በከፍተኛ ድረጃ የቀነሰ ነው ቢሉት ትችቱ ሲበዛባቸው 55 ምክትል ሚ/ሮችን ድልኤታዎችን የባለስልጣን ቁጥርን በመቀነስ ወጭን እቀንሳለሁ ቢሉም በመሾም አልሸሹም ዞር አሉ ሆኖባቸዋል ታይቶ የማይታወቅ ባለስልጣናትን ሾሙና አረፉት። ያም ሆኖ ግን በኔ አውቅልሃለሁኝ ትክክልኛ ምርጫ እስካልተደረገ ድረስ ሹመቱ ብዙዎችን ሊያስደስት አይችልም

Friday, November 2, 2018

የኢኮኖሚ ፖሊሲ ማሻሻያ አስፈላጊነት በኢትዮፒያ

የምጣኔ ሃብት ማሻሻያን የማድረግ አስፈላጊነት " ፦

የፋይናንስ ዘርፉ ለኢኖቬሽን (ለስራና አዳዲስ ቴክኖሎጂ ፈጠራ) እንቅፋት መሆኑ ተገለፀ።  የሃገራችን የፋይናንስ (በተለይም የባንክ፥የኢንሹራንስ) ዘርፍ በአፍሪካ አቅም እንኩዋን ተወዳዳሪ አይዶለም። ቅርባችንን ኬንያን ብንወስድ እንኩዋን ያደገ የፋይናንስ ዘርፍ ያላት ሲሆን ያደገ ያክስዮን ገበያ እንዲሁም የሃገሪቱ ባንኮችና ኢንሹራንስ ድርጅቶች በአፍሪካ ተወዳዳሪ ሲሆኑ በምስራቅ አፍሪካ ደቡብ ሱዳንና ኡጋንዳ ድረስ ሄደው መስራት የሚሉ ባንኮች እና የፋይናንስ ተቁዋማት ባለቤት ነች። ብድር ማግኘትም የኛን ሃገር ያህል ከባድ አይደለም በሞባይል ስልኮች የባንክ ብድርን መጨረስ እሚያስችል የቴክኖሎጂ አቅም አላቸው። በሃገራችን GDP የኬንያን ያለፈ ሲሆን በውጭ ኢንቨስትመንት በመሳብ ኢትዮፒያ ኬንያን አልፋለች። ይህ ሁሉ ግን ተወዳዳሪ የሆነ የባንክ ስርአትን ይፈልጋል። ይሁንና ገዥው ፓርቲ የዚህን ዘርፍ ክፍት ለማድረግ ፈቃደኛ ካለመሆኑም በላይ ሃገሪቱ የWTO ያለም የንግድ ድርጅት አባል እንዳትሆን እንቅፋት ሆኖአል።
በርካታ የኢንዱስትሪ ፓርኮች ባገሪቱ ተከፍተዋል እነርሱም ያገር ውስጥ ብቻ ሳይሆን ያካባቢውንና ያለም አቀፍ ገበያን ይፈልጋሉ ምርቶቻቸውን ለመሸጥ። የWTO አባል መሆን ኢንዱስትሪዎቹ በቀላሉ የአለም አቀፍ ገበያ ውስጥ እንድትገባና በከፍተኛ የውጭ ብድር የተሰሩት ኢንዱስትሪ ፓርኮችን በመጠቀም ሃገሪቱ ብድራን እንድትከፍል ያስችላታል። ነገር ግን ፓርኩን መስራት ብቻ ሳይሆን ማሻሻያዎችን በማድረግ ፓርኮቹና ምርቶቻቸው በአለም አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪ ለመሆን ያስችላቸዋል ።

Saturday, October 6, 2018

ኢህአዴጋውያንና ስፓርታውያን

የግዥው ፓርቲ ኢህአድልግ ከጥንታዊው የግሪክ ስፓርታውያን ጋር ተመሳሳይ ታሪክ እንዳለው ያውቃሉ ?
ይሁንና በታሪክ ከጥንት ግሪካውያን ስፓርታውያን በወታደራዊ ሃይላቸው ይታወቁ ነበረ። በተለይም የገነቡት እግረኛ ሃይል። በዘመኑ በዓለም ተወዳዳሪ አልነበረውም ግሪክ ከፐርሽያ ጋር ባደረገችው ጦርነት የባህር ሃይሉዋ ከፐርሽያን ድል ካደረጉ በሁዋላ ወደ ባህር ንግድ በማዞር ህልውናዋን ስታስጠብቅ ስፓርትስ ግን ይህን ጦርነትን ብቻ የሰለጠነ ሃይሉዋ ወደ ሌላ ምርታማ ዘርፍ ማዞር ስላልቻለች እንድው አቴናውያን ህልውናዋን ማስጠበቅ ስላልቻለች ልትከስም በቅታለች።