Thursday, February 28, 2019

ህገ_መንግስት ኢንሹራንስ ሰምተው ያውቃሉ

ሕገ መንግሥት ተርጓሚው አካል ከዚህ መሠረታዊ የፍትሕና ርትዕ መርህ በመነሳት፣ ለየትኛውም ወገን ባለማድላት ተጥሰዋል ተብሎ የቀረበለትን የሕገ መንግሥት መርሆዎች ለማፅናትና ለማስከበር ገለልተኛ መሆን ይገባዋል፤ በዚህ መርህ መሠረትም ተርጓሚው አካል እጅግ ወሳኝ ሚና የሚጫወት መሆኑን መገንዘብ አስፈላጊው ነው፡፡

ሌላው ሕገ መንግሥትን ከመተርጎም አንፃር አዲስ ክስተት ወይም ጽንሰ ሐሳብ የሆነው የሕገ መንግሥት ኢንሹራንስ የሚለውንም አስፈላጊነትን ማንሳት ያሻል፡፡ ሕገ መንግሥት ተርጓሚው አካል በተለይ የመድበለ ፓርቲ ሥርዓት በሚከተሉ አገሮች ውስጥ፣ ለተፎካካሪ ፓርቲዎች ዋስትና የሚሰጥ አካል እንደሚሆን ይታወቃል።፡

‹‹የመድበለ ፓርቲ ሥርዓት የሚከተል የፖለቲካ ሥርዓት ውስጥ በዴሞክራሲያዊ ምርጫ ፓርቲዎች ይቀያየራሉ፡፡ ስለሆነም አንድ ፓርቲ ከሥልጣን ከወረደ በኋላ ምንም አድልኦ በሌለበት ሁኔታ በሚቀጥለው ምርጫ የምረጡኝ ቅስቀሳና ዘመቻ አድርጎ ወደ ሥልጣን እንዲመለስ ዋስትና ያስፈልገዋል፡፡

አማርኛ የAU የስራ ቁዋንቁዋ ሆነ

የአውሮፓ ህብረት #EU ከአስር በላይ የስራ ቁዋንቁዋዎች ሲኖሩት፥ የአፍሪካ ህብረትም አማርኛ ከአረብኛ ከእንግሊዝኛ ከስዋሂሊና ከፖርቱጋል እና ከፈረንሳይኛ ቀጥሎ 6ኛ የስራ ቁዋንቁዋ ይሆን ዘንድ አማርኛ ቁዋንቁዋን ሰይሞአል።  ከአስሩ አፍሪካውያን አንዱ ኢትዮጲያዊ ሲሆን የህዝብ ብዛቱዋ ከአፍሪካ 2ኛ የሆነ ህዝብ መግባቢያ ቁዋንቁዋ የሆነው አማርኛ ቁዋንቁዋ የAU one of the official languages of AU መሆኑ አኩሪ ሲሆን የጠ/ሚሩ ድል ነው።
ይህም ለበርካታ ኢትዮጲያውያን የስራ እድልን ሲፈጥር የኢትዮጲያውያን ደራሲዎች በአማርኛ ብቻ ነው እሚጽፉት በአውሮፓውያን ቁዋንቁዋ እንደ ኬንያ ጋና ወይም እንደ ናይጄሪያና ደቡብ አፍሪካ ደራስያን  በእንግሊዝኛ ቁዋንቁዋ ቢጽፉ ኖሮ አለም ኣቀፍ እውቅናን ይጎናጸፉ ነበር ለሚለው ምላሽን የሚሰጥ ነው። ምክንያቱም በርካታ ኣፍሪካውያን የአማርኛ ቁዋንቁዋን እሚማሩ ከሆነ የኢትዮጲያ ቁዋንቁዋ ፥ ስነ-ጽሁፍና ባህል ሰፊ የመተዋወቅ እድልን ያገኛክ።

Wednesday, February 6, 2019

trade war USA Vs China

የአሜሪካና የቻይና የንግድ ጦርነት #Trade war ወደ ገንዘብ ምንዛሪ ጦርነት # Currency war ይቀየራል ተብሎ ተሰግቶአል። ይህ ደግሞ የሌላውን አገር ሆነ ብሎ# የገንዘብ ምንዛሪን ከፍና ዝቅ እንዲል በማድረግ የዝያን ሃገር ገንዘብ #ማክሰርና ዋጋ ማሳጣት ማለት ሲሆን ይህ በትራምፕ የተቀሰቀሰው የንግድ ጦርነት አለምን በተለይም ታዳጊ ሃገራትን ክፉኛ ሊጎዳ ይችላል። እልኽኛው #Stubbourn ግትሩ # ፕሬዝደንት ትራምፕ ገና ከዚህ የባሰ #ማዕቀብን #በቻይና ላይ ለመጣል እየተዘጋጁ ነው።
አሜሪካ ከዚህ ቀደም ባላንጣ ያለቻቸውን ቱርክንና ሩስያን ገንዘብ ምንዛሪን ዋጋ በማሳጣት የስራ አጥ Unemployment rate #ቁጥሩ እንዲጨምር ፥ #ኤክስፖርት እንዲቀንስና ማህበራዊና ፖለቲካዊ ቀውስን እሚያስከትልና መንግስታትን እሚያናጋ ነው። ቻይናም የስራ አጥ ቁጥሩዋ እየወነሰ ሲገኝ ይህን የንግድ #ጦርነትን ተከትሎ ለመጀመርያ ግዜ #በ30 አመታት ውስጥ የኢኮኖሚ #እድገትዋ #ቀንሶአል።