Thursday, August 15, 2013

Jews and the Bible


ጦርነት የሌለበት ስርአትን ለማሰብ አዲሱን የአለም ስርአትን ማሰብ ሳይቀል አይቀርም ። በአለም ላይ ሀገራት እስካሉ ድረስና ሀገራት በድንበር ፣ በሀይማኖት በርእዮተ-ዓለም ፣ በኢኮኖሚና በብሄራዊ ጥቅም እስከተለያዩ ድረስ በአለም ላይ የጦርነት ስጋት መኖሩ አይቀሬ ሆኖ ይታያል ።
በመፅሀፍ ቅዱስ ላይ ከ188 ያላነሱ ሴቶች መጠቀሳቸውን የመፅሀፍ ቅዱስ ምሁራን ይገልፃሉ ። መፅሀፍ ቅዱስ አፈንጋጭ ለሆኑ ሴቶች የተደረገባቸውንነም ቅጣትንም ይገልፃል ። ለምሳሌ መግደላዊት ማርያም ከአሮን ጋር ሆና ሙሴ ኢትዮጲያዊቷን በማግባቱ ምክንያት ሙሴን በመናገሯ ምክንያት እግዝአብሄር እጅግ ተቆጥቶ እንዴት ባሪያዬን ሙሴን ትናገሪያለሽ በማለት መግደላዊት ማርያም በመጨረሻም በምድረ በዳ እንደሞተች እንዲሁም እግዝአብሄር በሷ ምክንያት ለሰባት ቀናት እስራኤላውያን ጉዟቸውን እንዳዘገዩም መፅሀፍ ቅዱስ ይገልፃል ።
እንዲሁም ኤዛቤል የተባለች እንዲሁ ባእድ አምልኮን በመከተል ፣ በማምለክና በክፋት የምትታወቅ ሴት በመጨረሻ አስከሬኗን ውሻ እንደበላው ይገልፃል ። በእርግጥ ኤዛቤል የእስራኤል አምሳያ ነች ጣኦትን ማምለክ የጀመረችውና ለእግዝአብሄር አልታዘዝ ያለችውን እየሩሳሌምን ይወክላል ። እስራኤልም ሩትና ሁለት ሴቶች እስራኤል የመሰረቱት ናቸው ። እብራውያን ምእራፍ 12 ቁጥር 22 ።
መፅሀፍ ቅዱስ በተመለከት ቮልቴር አይሁዳውያንን ሲተች «እውራን ተርጓሚዎች» ይላቸዋል ፣ ቮልቴር እንደሚለው እኛ አውሮፓውያን ስናቃጥላቸውና በተገኘው ምክንያት ሁሉ ጥፋተኛ አድርገን ስንቀጣቸው የነበሩት አይሁዳውያን የእግዝአብሄር በእነርሱ በኩል መገለጡ ያስገርመዋል ።
ይህ ብቻም ሳይሆን ቮልቴር አዲስ ኪዳን እርስ በእርሱ የሚጋጭ ስለሆነ የትኛውን እንዳለብን ግልፅ አይደለም ይላል ። ለቮልቴር ሀይማኖተኛና ስነ-መለኮተኛ የተለያዩ ናቸው ። እንደ ቮልቴር አገላለፅ ለአለም በሀይማኖት የተነሳ ለተከሰቱ ግጭቶች ተጠያቂዎቹ ስነ- መለኮተኞች ስለሆኑ ነው የሚል አቋም አለው  ። ሀይማኖተኛ ጦርን አይመዝነም ማለቱ ነው በተዘዋዋሪ መንገድ ። ለቮልቴር በአለም ላይ ያሉ ካህናት ፣ ሰባኪዎች ፣ ፓስተሮች ወዘተ ሰነ- መለኮታውያን ናቸው እንጂ ሀይማኖተኞች አይደሉም ። ለቮልቱር ስነ - መለኮታውያን ማለት ልክ እንደ አንድ ርእዮተ አለም አራማጅ ማለት ነው ። በአለም ላይ በአሜሪካን በቀድሞዋ ሶቭየት ህብረት ፣ በአሜሪካና በኮሚኒስት ቻይና መሀከል እንዳለው አይነት የአስተሳሰብ ወይም የአስተምህሮ «የዶክትሪን» እና የቀኖና «ዶግማ» ልዩነት የሚንፀባረቀው የአለምን ሀይማኖት የሚመሩት ስነ-መለኮታውያን ስለሆኑ ነው ባይ ነው ። 

ሀዋርያው ጳውሎስ ትኩረቱን የደረገው በእምነት ዙሪያ ሲሆን በህግ አልታሰርንም ፣ በህግ አልተፈረደብንም የሚል አስተምህሮዎቹን ለበርካታ በግሪክ ዙሪያ ለነበሩ ህዝቦች፣ እንዲሁም ለጣሊያንና ለስፔንም ጭምር በላካቸው መልእክቶቹ ላይ አስርፍሮ ልኳል ። አይሁዳውያን የሙሴን ህግጋት አጥብቀው የሚከተሉ ሲሆን በዋነኛው መፅሀፋቸውም በታልሙድም ጭምር የአይሁድ እምነትን የማይከተሉትን ሁሉ እንደ ዝቅተኛ ሰው ዘር አድርጎ የሚቆጥር ነው ። ጳውሎስም በመልእክቱ በረከት የመጣው በአይሀዳውያን ስለሆነ አይሁዳውያንን እነዲ ንዲባርኩ ለተከታዮቹ ክርስትያኖች በመልእክቱ አስተላልፎ ነበበረ ።

የአፍሪካ ህዳሴ


በዓለም ላይ ከዚህ በፊት ታይቶ በማይታወቅ ሁኔታ ዘመኑ ወደ አፍሪካ ያዘመመ ሆኖ መታየት ጀምሯል ። ለአንዱ ሲዘንብ ለሌላው ያካፋል እንዲሉ ለቻይናና ለሌሎች የደቡብ መስራቅ እስያ ያካፈው የስልጣኔና የምጣኔ-ሐብት ብልፅግና ለመጀመሪያ ጊዜ ለአፍሪካም ማካ ፋት ጀምሯል ።
      ለአፍሪካ አህጉር ድህነት ብቸኛው ዋና ምክንያት ባይሆንም አንዱ ምክንያት በርካታ የአፍሪካ አገራት በባርነት ፣ ከዚያም በቅኝ ግዛት አገዛዝ ስር መውደቃቸው ለአህጉሩ መደህየት አንዱ ምክንያት መሆኑ አያጠራጥርም ። አፍሪካ ነፃነቷን ካገኘች በኋላም ቢሆን በአብዛኛው ስለ ፖለቲካ ፣ አስተዳደርና ስለ ምጣኔ-ሀብት ስለ መሳሰለው ጉዳይ እውቀት ባልነበራቸው ወታደራዊ መሪዎች እጅ ስልጣኑ በመግባቱ ምክንያት ከ1960ዎቹ ጀምሮ እስከ 2000ዎቹ ጅማሮ ድረስ ብዙዎቹ አፍሪካ አገራት ጉዞ የኋሊት ሆኖ ቆይቷል ።
      ነገር ግን የደቡብ ምስራቅ እስያ ሀገራት ማንሰራራት ከጀመሩ ወዲህ ከእድገቱ ፀበል ለአፍሪካ አገራት መድረስ ጀምሯል ። የምጣኔ-ሐብት እድገት ለአንድ አገር ጅማሮ ሲሆን ለዛ ሀገር ወደፊት በሌሎች ዘርፍ ለሚያስመዘግበው እድገት መደላድሉ የምጣኔ-ሐብት እድገቱ ነው ። ለአንድ ስልጣኔ ኢኮኖሚ መሰረት ሲሆን ከኢኮኖሚ እድገት ብቻ ግን እድገት ያበቃል ማለት አይደለም ።  በብዙዎቹ የአፍሪካ አገራት መሪዎች ካለፉት ስህተቶቻቸው በመማር ከመቼውም ጊዜ በተሻለ አመራርን መስጠታቸው መታዘብ ይቻላል ።
      የአፍሪካ አገራት ለዚህ አስፈጊውን ስልጣኔ መሰረት በመጣል ላይ መሆናቸው መልካም  ዜና ነው ። ነገር ግን እንደሚታወቀው አንድ ስልጣኔ በኢኮኖሚ እድገት ብቻ አያበቃም ከዚያ ይልቅ አንድ ጊዜ የሰዎች መሰረታዊ ፍላጎቶች ከተሟሉ በኋላ ግን መንፈሳዊ ፣ ስነ-ልቦናዊ ባህላዊ ሀይማኖታዊ እና ፖለቲካዊ እና ሀሳብን የመግለፅ ነፃነቶቻቸውን የመሳሰሉ ከፍ ያሉ ፍላጎቶቻችቸውን ወደ ማሟላት መሄዳቸው አይቀርም ።
ለዚህ አይነተኛ ምሳሌ የምትሆነው ቻይና ስትሆን ይህቺ ሀገር ምጣኔ ሀብቷን በአስደናቂ ፍጥነት በሀያና ሰላሳ አመታት ውስጥ ወደ ግዙፉ ምጣኔ ሀብት ስትቀይር በአንፃሩ የፖለቲካ አድተዳደሯ ግን በአንድ ፓርቲ ላይ የተመሰረተ ሆኖ መቀጠሉ ለወደፊት መረጋጋቷ ስጋትን መደቀኑ አይቀርም ። ነገር ግን በርካታ ተመልካቾች እንደሚገምቱት የመካከለኛው መደብ በቁጥና ፣በሀብት እየበረከተ ሲሄድ ተጨማሪ የፖለቲካ መብቱን መጠየቁ አይቀርም ። ከአንድ ሺህ በላይ የሚሆን ወጣት ትውልዷን እ.አ.አ. በ1989 ዓ.ም. በታይናሚን አደባባይ ባደረጉት የተቃውሞ አመፅ የፈጀችው ቻይና እየበለፀገ ያለው ወጣት ህዝቧ የበለጠ የመናገር ነፃነትን ፣ የመምረጥ ሀሳብን የመግለፅ የመሳሰሉ ዲሞክራሲያዊ መብቶቹ በበለጠ እንዲከበሩለት መጠየቁ አይቀርም ።  
      ምእራባውያን ከላይ ከላይ ሲታይ ስልጣኔአቸው በቁሳዊ ፍላጎቶቻቸውን በማሟላት ላይ የተመሰረተ ቢመስልንም ወደ ውስጡ ሲገባ ግን ስልጣኔቸው የተመሰረተው በጣም መሰረታዊ በሆኑ ፍልስፍናዎች አስተሳሰቦችና አስተምህሮቶች ላይ ነው ። ከእነኚህ መሰረታዊ ከሆኑ የፖለቲካን ሆነ የህግ የምጣኔ ሀብት አስተምህሮዎቻቸው ዝንፍ የማይሉ ሲሆን ችግር ቢያጋጥማቸው እንኳን ጊዜ ሰጥተው መልሰው ነገሮችን ወደ ነበሩበት ያስተካክሉታል ።
      ምንም አስንኳን በ20ኛው ክፍል ዘመን ላይ የአለም ሀያሏ አገር አሜሪካ ብትሆንም አሜሪካንን የመሰረቱ መስራች አባቶቿ ግን ያቺን አገር መሰረት የጣሉት በአውሮፓውያን ፈላስፎች አስተረምህሮና ፍልስፍና ላይ ነው ። እንደ ጆን ሎኬና ፣ሩሶን በመሳሰሉ የእንግሊዝና ፈረንሳይ ፈላስፎች አስተምህሮዎች ላይ ነው ። በአብርሆት ዘመን ከአውሮፓ እንደ ዋና አሳብያንና ፈላስፎች ይቆጠሩ የነበሩት በተለይም የፈረንሳይ እንግሊዝ ፈላስፎችና ፀሀፍት ነበሩ ። አሜሪካ በምትመሰረትበት ወቅት በአለም ላይ ተሰሚነት የነበራቸው የአውሮፓውያን አሳብያን ነበሩ ። በመሆኑም አሜሪካ የእነሱን አስተምህሮ በመውስድ ራሷን እንደ አገር በሁለት እግሯ መቆም ችላለች ።

የመንፈስ ህልውና


በሚሊየን አመታት ውጥ የሰው ዘር ራሱ ህልውናውን ሊያጣ ይችላል ። በዚህ ምድር ላይ የምናየው ነገር በጊዜ ውስጥ ሊፈራርስና ሊጠፋ እንደሚችል መገመት ይቻላል ።
በምእራባውያን የስልጣኔ አስተሳሰብ መሰረት ስልጣኔ ከተጀመረ ቢበዛ አስር ሺህ አመታት አይበልጥም ። የምስራቁ ቅድመ-ታሪክ የሚባለውን የሚያጠቃልል ሲሆን በአንፃሩ የምእራበውባውያን ስልጣነቤ ኔም ሆነ አስተሳሰብ ከዘመናዊው ውምን ወይንም በስነ-ሰብ «አንትሮፖሎጂስቶች» ተመራማሪዎች  ከተደረሰበት የምርምር ውጤት አያልፍም ። ይህም ማለት በአብዛኛው የሰው ልጅ እርሻን ጀምሮ የቤት እንሰሳትን አርብቶ መኖር ከጀመረበት ዘመን የሚጀምር ነው ። ነገር ግን ቅድመ-ታሪክ ከዚያም ያለፈ ሲሆን በመቶ ሺዎች አመታት የሚ ቆጠር እድሜን ያስቆጠረ ነው ።  
መንፈስን በተመለከተ አይሁዳውያን ፣ ኢራናውያን (ፐርሺያኖች) እና አረቦች እና ህንዶችናቸው ሊቃውንቱ ። በአብዛኛው ምእራባውያን ቁሳዊ ነገርን በመፍጠር ረገድ ተወዳዳሪ የላቸውም ። ምእራባውያና ባሏቸው ወፈ - ሰማይ ኩባንያዎቻቸውና ኮርፖሬሽኖቻቸው አማካይነት በአለም ላይ ግዙፍ ምጣኔ-ሐብት እንቅስቃሴ ባለቤቶች ሲሆኑ በአንፃሩ መንፈሳዊ ነገርን በተመለከተ ግን ከምስራቅ ሰዎች ብዙ የሚማሩት ነገር አለ  
በአንፃሩ ቁሳዊ ነገርን በመፍጠር ረገድ ግን ምስራቆቹ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ከምእራባውያን በመማር ምጣኔ-ሀብታቸውን ማሳደግ እና በኢንዱስትሪ መበልፀግ የጀመሩት አሁን በቅርብ ነው ማለት ይቻላል ። ለዚህም በአንድ በኩል ቀድመው በሳይንስና ቴክኖሎጂ የበለፀጉት ምእራባውያን ቀድሞ አፍሪካውያንን በባርነት ፣ በኋላም አፍሪካንና እስያን በቅኝ ግዛት በመ  ግዛት ለመቶዎች አመታት ወደ ኋላ እንዳያድጉ ማነቆ ስለሆኗቸው ሲሆን ፣ በኋላ ላይም ቢሆን እነኚህ በምእራባውያን አጠራር «ሶስተኛው ዓለም» በመባል ሲጠሩ የነበሩት መጀመሪያ ለይ ላይ የአገሮቻቸውን አስተዳደሮች ከቅኝ ገዢዎች በተረከቡባቸው ወቅቶች ካለማወቅና ብሄራዊ ስሜታቸውን ለማነቃቃት በአንዛኛው ትክክለኛውን የእድገትና የልማት ጎዳናን ሳይከተሉ በመቅረታቸው ምክንያት ከምእራባውያን አይነት የዳበረ እድገትን ለአስርት አመታት መፍጠር አቅቷቸው ቆይተዋል ።
ሀያልና ግዙፍ ኢኮኖሚን በሀያና በሰላሳ አመታት ውስጥ የገነባችና ቻይናን  ብንወስድ ቻይና በማኦ የአገዛዝ ዘመን በባህል አብዮት እድገት ገጠር ነው ያለከው በሚል የተማረውን ሀይሏን ወደ ገጠር በመላክ በሚሊዮን ዜጎቿን ለእልቂት ስትዳርግ ምጣኔ ሀብቷም የሶስተኛው አለም ከሚባሉት ሆኖ ቀርቶ ቆይቷል ። ቻይና ከማኦ ህልፍት በኋላ በዴንግ ዚያዎ ፔንግ ዘመን «ድመቷ ጥቁት ወይም በነጭ መሆኗ ሳይሆን ፣ ድመት መያዝ መቻሏ ነው» በሚል አለመካከት ካፒታሊዝምም ሆነ ሶሻሊዝም ዋናው ምጣኔ ሀብቱን ማሳደጉና የህዝብን የኢኮኖሚ ጥያቄን መመለሱ ነው በሚል ተግባራዊ «ፕራግማቲክ» በሆነ አስተሳሰብ ወደ ካፒታሊዝም የኢኮኖሞ ስርአት በመግባት ምእራባውያን ለመድረስ በርካታ መቶ አመታት የፈጀባቸውን በሀያና ሰላሳ አመታት ውስጥ ማሳካሰት የቻለችው ። ቀድሞ ታዳጊ ይባሉ የነበሩት አገራት ወደ ቁሳዊ እድገት ፈጠራ ከገቡ ምእተራባውያንን በቀላሉ ማለፍ እንደሚችሉ ቻይናና ሌሎቹንም ተመሳሳይ የእድገት ጎዳና  ውስጥ የገቡት «ብሪክስ» በመባል የሚታወቁት አገራት አይነተኛ ምስክሮች ናቸው ።      
ብላስቶቭስኪ የተባለችው የአዲሱ ዘመን እንቅስቃሴ መስራች ራሺያዊት እንደምትለው ምእራባውያን ለህንዳውያን መፋንፈሳውያን የበላይነትን መቀለበል አለባቸው ።
በነገራችን ላይ አፍሪካውያንና እስያውያን ከተፈጥሮ ጋር ያላቸው ትስስር እጅግ ጠንካራ ነው ። ለምሳሌ በቻይና አንድ ቤሄረሰብ አንድ ልጅ ሲወለድ አንድ ዛፍ የተ ይተከልለታል ፣ ልክ ያ ሰው ሲሞት ሲወለድ የተተከለለት ዛፍ ተቆርጦ የአስከሬን ሳጥን ይሰራበትና ይቀበርበታል ። ዛፉም ለዛ ሰው የተተከለ እንደመሆኑ ማንም ሰው አይቆርጠውም ። ለደኑ በየጊዜው የአምልኮ ስርአትን የሚያደርጉለት ሲሆን አካባቢውም በደንና በጫካ የተሸፈነ ሲሆን ደናማው አካባቢ በመባል በቻይና ይጠራል ። አፍሪካውያንም ተፈጥሮን የማይነኩ ሲሆኑ ከሚበሉትና ከሚጠጡት ውጪ ደኑን የማይነኩትና ጉዳትን የነማያደርሱበት ሲሆን ጥቅጥቅ ካለው ደን ጋር ጎን ለጎን በሰላም ለዘመናት ሲኖሩ ቆይተዋል ። በአማዞንም ደኖችም ውስጥ እንዲሁ ጥንታዊና ቀደምት የሆኑት የአማዞን ነዋሪዎች ከተፈጥሮ ጋር ለሺዎች አመታት በሰላምና ተፈጥሮውን ሳይነኩት ኖረዋል ።
አንድ ሰው እነኚህን ሰዎች ባእድ አምላኪዎች ናቸው ሊል ይችላል ፣ ነገር ግን ከተፈጥሮ ጋር ተግባብተው ለሺዎች አመታት መኖር መቻላቸውን ማየት ይገባል ። በአሁኑ  ዘመን ሳይንስና ቴክኖሎጂ ባደገ ቁጥር በተፈጥሮ ላይ የሚደርሰው ጉዳትም እያየለ ሲሄድ በተለያዩ አገራት የሙቀት መጨመር ፣ የጎርፍ መጥለቅለቅ ፣ የዓለም ሙቀት መጨመር ፣ የአካባቢ መጎዳት ፣ የአፈር አሲዳማ መሆን ፣ የአሲዳማ ዝናብ መጣል፣የውቅያኖስና የውሀ አካላት መጠን መጨመርና በሰሜንና በደቡብ ዋልታዎችና በተራራዎች አናት ላይ ያለ በረዶ መቅለጥ እየታየ ነው ። ይህም ዘመናዊው ሰው በእውቀቱ ተፈጥሮን በመቃረኑ የተከተለ መሆኑ አያሻማም ። የሰው ልጅ በገዛ ራሱ አስቦና ተጨንቆ የፈጠረው እውቀቱ ጠላቱ ሊሆን እንደሚችል ለመረዳት በአካባቢ ላይ የሚደርሰውን ጉዳት በማየት በቀላሉ መረዳት ይቻላል ።    
         

ሄግል


ሱን ሱ የተባለው ጥንታዊ የቻይና ፈላስፋ የሰዎች ክፋት የሚወገደው በትምህርት ነው ይላል ። በምእራቡ አለም ታዋቂ አርቲስቶች በአንድ በኩል በንግድ በቢዝነስ ፣ በሌላ በኩል ደግሞ ለረጅም ጊዜ የሚቆዩ ስራዎችን ነው እሚሰሩት ። ይህም በአንድ በኩል ለረጅም ጊዜ የሚቆይ (Timeless) የሆነ ስራን እሚሰሩ አርቲስቶች ረጅም ጊዜ የሚቆይን ስራን ሊሰሩ እድል ያገኛሉ ። ነገር ግን ለንግድ ወይም ለገቢ ብቻ ብለው ስራን እሚሰሩ ግን ስራቸው የአንድ ሰሞን ብቻ ሆኖ ይቀራል ።
የማስታወቂያ ስታዎችን ብንወስድ በእኛ ሀገር በአርቲስቶች የሚሰራ ሲሆን በሌላው አለም ግን በሰለጠኑ የገበያ ባለሙያዎች ነው እሚሰራው ።
አራቱ እውቀት እሚሰበሰብባቸው መንገዶች ምልከታ (Observation) ፣ ነገሮችን የማየትና የመረዳት ችሎታ፣ የማሰብ ችሎታ ፣ እርግጥ የማስታወስ ችሎታ በላይ የማሰብ ችሎታ የበለጠ ነው ። ማንም ሰው ሊያስታውስ ቢችልም ያንን ነገር በተለየ መንገድ የማሰብ ችሎታ ግን የተለመደ አይደለም ። በአለም ላይ የምናያቸው በርካታ ታላላቅ ነገሮች የተፈጠሩት የማሰብ ችሎታ ባላቸው ሰዎች ሲሆን ።
የማስታወስ ችሎታ፣ ትምህርትና ብዙ ማንበብ ፣ ሲሆኑ እነኚህ ሁሉ ነገሮች ቢኖሩም ለአንድ ሰው ስኬታማ እንዲሆን ትጋት (ዲሲፕሊን) መሰረት ነው ። ሶስቱ ምልከታ «ኦብዘርቬሽን» ሙከራ «ኤክስፐርመንቴሽን» እና እነ ኒውተን እና ሌሎች የአብርሆት ዘመን ፈላስፎች የዘገቡት

የወንዶች ዓለም ክፍል -2


በብዙ እንሰሳት ውስጥ የወንዱ ቦታ ጎላ ሊል ይችላል ። በአንበሳ ብንመለከት ዋናውን አደን  የምታከናውነው ሴቷ አንበሳ ስትሆን ፣ በአንፃሩ ወንዱ አንበሳ ብዙውን ጊዜ አያድንም ። ሴቷ አንባሳ  የሚያስቸግር ነገር ሲመጣ ካልሆነ በስተቀር ወንዱ ብዙም በአደን አይሳተፍም ። ይሁን እንጂ አንድ አነስተኛ የአንበሳ መንጋ የሚመራውም ሆነ ጥበቃ የሚደረግለት በወንዱ አንበሳ አማካይነት ነው ። ይሁን እንጂ ይህ በአንበሶች ዘንድ «የፖለቲካ» ችግር የለም ።
ሜሪቶክራሲ ከሴቷ ይልቅ የወንዱን የበላይነትን የሚያጠናክር ነው ። በአብዛኛው ሜሪቶክራሲ ውስጥ መወዳደር የሚችለው የተሻለ የመወዳደር አቅምን የሚሰጠው ለወንዱ ነው ። ይህም አንዱ በወንዱና በሴቷ መሀከል የበዛ የሰፋ  ልዩነት እንዲፈጠር ካደረጉት ነገሮች አንዱ ይሄው ነው ።
አንዳንድ ዘርፎች በአብዛኛው በወንዶች ብቻ የተያዙ አሉ ። ለምሳሌ የሲልከን ቫሊ ፣ ዎል ስትሪትና ብንመለከት በአብዛኛው ወንዶች ናቸው ። እንዲሁም ፊፋን ብንወስድ ፊፋ «የወንዶች ክበብ» ነው ይባላል ።
እንደ ስካንዴበኒቪያና አንዳንድ የእስያ ሀገራት ሴቶች በአንፃራዊነት ከወንዱ ጋር የሚመጣጠን ስፍራን ይዘው ይገኛሉ ። በአብዛኛው ለሴቶች ከወንዱ ይልቅ አለማደግ ምክንያቱ በስራቸውና በቤተሰባቸው መሀከል አመጣጥኖ መጓዝ መቻል ለብዙ ሴቶች  ፈተና እንደሆነ ብዙ ተመራማሪዎች የደረሱበት ጊዳይ ነው ።