Tuesday, July 3, 2018

liberalisation & privatization in Ethiopia, ethiopian airlines ወደ ግል ከመዛወሩ በፊት የኤርፖርቶች ድርጅት ከኢትዮጲያ አየር መንገድ ግሩፕ መለያየት አለበት


በደፈናው የልማት ድርጅቶችን ወደ ግል ማዛወር የሚያስከትለው ችግር
ጸሃፊው ስሜነህ ተረፈ
ኢ -ሜይል smofed@gmail.com ወይም
መንግስት በቅርቡ ትላልቅ የመንግስት የልማት ድርቶችን ወደ ግል ለማዛወር መወሰኑ ተሰምቷል ፤ ይህ የፕራይቬታይዜሽን ሂደት መምጣቱ እሰየው ቢሆንም ነገር ግን መንግስት ሊጠነቀቅና ሊያጠናቸው የሚያስፈልጉ ጉዳዮች አሉ ከእነኚህም አንዱ በ2009 ዓ.ም በወጣው የኢትዮጲያ አየር መንገድ ግሩፕ ማቋቋሚያ የሚኒስትሮች ምክር ቤት ደንብ ቁ / 406 ፤ 2009 ዓ.ም መሰረት በተደራጀው የኢትዮጲያ አየር መንገድ ግሩፕ በስሩ የኤርፖርቶች ድርጅትንና እንዲሁም ርካሽ የሰው ሃይልን በመጠቀም በሃገር ውስጥ የአውሮፕላን የተለያዩ አካላትን መፈብረክና መጠገን ለቦይንግና ለኤርባስ ለሌሎችም ኩባንያዎች የምርት አካላት መገጣጠሚያ ማእከልን በባለቤትነት መያዝን የሚያጠቃልል ነው ፤ ኤርፖርቶችን መገንባትና መጠገን፤እንዲሁም ኤሮኒተካል አገልግሎቶችንና ኤሮኖቲካል ያልሆኑ አገልግሎቶችን መስጠት ለኤር ኦፕሬተሮች የሚሰጡ አገልግሎቶችን መስጠት፤ የአቪየሽን ባለሙያዎችን ማሰልጠንን ቀድሞ በኤርፖርቶች ድርጅት እና በሲቪል አቪየሽን ባለስልጣን ይሰሩ የነበሩ ስራዎች ሁሉ ለአየር መንገድ ግሩፕ ተሰጥተዋል በዚህ ደንብ መሰረት የግሩፑ የተከፈለ ካፒታል 31.2 ቢሊየን በር ሲሆን የተፈቀደው ካፒታል ደግሞ 100 ቢሊየን መሆኑ ተገልጧል፡፡
 በመጀመሪያ የኢትዮጲያ አየር መንገድ የአየር ትራንስፖርት ሰጪ ድርጅት እንደመሆኑና ኤርፖርቶችን ማስተዳደርና መገንባት፤ ማስፋፋት፤መጠገን ፤ የአየር ትራፊክን መቆጣጠር እና የአውሮፕላን አካላትን መገጣጠም ስራ በሃገር ውስጥ መሰራት መጀመሩ መልካም ቢሆንም ራሱን የቻለ ድርጅት ሆኖ መቋቋም የነበረበት ነው እንጂ የአየር ትራንስፖርትን አገልግሎት የሚሰጠው አየር መንገድ እዚህ ውስጥ መግባት አልነበረበትም ፡፡ የምእራቡ ዓለም ታላላቅ ኩባንያዎች ኮር ቢዝነስ (Core Business) ማለትም የኩባንያው ዋነኛ ስራውና ዋናው የገቢ ምንጩ ከሆነውና በርካታ ባለሙያዎችና ልምድ፤ እውቀት ካለው ዘርፍ ማለትም የማጓጓዝ አገልግሎት ዘርፍ መውጣት አልነበረበትም ፡፡ ከዋናው ቢዝነስ የሚወጡ ኩባንያዎች የእነሱ ዋነኛ ሙያ ወዳልሆነው ዘርፍ በሚቀላቀሉበት ወቅት ለከፍተኛ ወጪና ኪሳራ የሚዳረጉ ሲሆን ዋናው ስራቸው ያልሆኑትን በማራገፍ ወደ ዋናው ስራቸው ሲመለሱ ተስተውሏል ፤ ዘርፉ ውድድር ያለበት እንደመሆኑ ትኩረቱ መሆን ያለበት በትራንስፖርት ዘርፍ ነው ፤ በዚህ ደንብ መሰረት አየር መንገዱ በሆቴልና ቱሪዝም ዘርፍ መሰማራቱና በሌሎች አየር መንገዶች ድርሻ መግዛቱ፤ቦንድ መሸጡ ያጠናክረዋል ከዚህ ውጭ ግን የሁለቱን ድርጅቶችን የስራ ድርሻን መጠቅለሉ ግን ተገቢ አይደለም ፡፡
በ2009 ዓ.ም በወጣው አዋጅ መሰረት ግን እነዚህን 3 የተለያዩ ድርጅቶች ይሰሩት የነበረውን ስራ የኢትዮጲያ አየር መንገድ ግሩፕ የሚል ስያሜ ከተሰጠው ድርጅት ጋር አለአግባብ የተቀላቀሉ ሲሆን የአየር ክልል ተቆጣጣሪ የሆነውን እንዲሁም ኤርፖርቶችን ከኤርፖርቶች ድርጅት ተከራይቶ የሚጠቀመው የኢትዮጲያ አየር መንገድን ከኤርፖርቶች ድርጅት ጋር ተቀላቅሏል ፡፡ ነገር ግን የኤርፖርቶ ድርጅት ኤርፖርቶችንና ተርሚናሎችን የሚሰራ ፤ የሚጠግንና የአየር ማረፊያ ሜዳዎችን ለአየር መንገዶች በማከራየት በርካታ ቢሊየን ብሮችን በየአመቱ ለመንግስት ገቢ የሚያደርግ ነው፡፡ ድርጅቱ የኮቴ በማስከፈል ገቢን የሚያኝ ሲሆን ፤ ከዚህም በተጨማሪ ወደ ሃገር ውስጥ የሚገቡና የሚወጡትን ደህንነትን መቆጣጠር ፤ መፈተሽ የመሳሰሉትን የደህንነት ስራዎችን የሚሰራ ነው ፡፡
ከዚህም በተጨማሪ በአየር ማረፊያ ግቢ ውስጥ ያሉ ሱቆችን ቢሮዎችንና የመኪና ማቆሚያዎችን በማከራየት እንዲሁ ለመንግስት ገቢን የሚያስገባ ሲሆን ሲጀመር ከኢትዮጲያ አየር መንገድ የተለየ በመሆኑ ከአየር መንገዱ ጋር መቀላቀል አልነበረበትም ፤ አየር መንገዱን ለማሳደግ ከተፈለገ እንኳን አሁን እንደወጣው ፖሊሲ የተወሰነ ድርሻን ወደ ግል ባለሃብቶች ማዛወር እንጂ መቼም ቢሆን የአገሪቷ ንብረት የሆኑትን ኤርፖርቶችን በማቀላቀል መሆን አልነበረበትም፡፡ ይህ የተለያየ አደረጃጀት ስራውንም የተለያየ በመሆኑ ሲሆን በቅርቡ በወጣው አዋጅ ግን ተቀላቅለዋል ውህደቱ በተፈጸመበት ወቅት የኢትዮጲያ አየር መንገድ ዋና ስራ አስፈጻሚ እንደገለፁት ይህ ውህደት ወደ ኢትዮጲያ አቪየሽን ግሩፕ ወደ ሚባል የአቪየሽን መስሪያ ቤትንም ጨምሮ አንድ እንደሚሆን ገልጸዋል፡፡
ነገር ግን የእነኚህ 3 ወሳኝ የሆኑ ነገር ግን የተለያየ ስራን የሚሰሩ ድርጅቶችን ከተዋሃዱ በኋላ የአየር ደህንነትንና የአውሮፕላኖችን አስተማማኝነትን የፓይለቶችን የሙያ ፈቃድ የሚሰጠው፤ የሚፈትሸውና ፈቃድን የሚሰጠው የሚቆጣጠረው የአቪየሽን መስሪያ ቤትና ስትራቴጂያዊ የሆኑትን የአውሮፕላን ማሳረፊያ ሜዳዎችን በንብረትነት የያዘው ተቋምን የኤርፖርቶች ድርጅትን ጨምሮ ወደ ግል ማዛወር ከሃገሪቱን ደህንነት ጭምር አደጋ ውስጥ የሚከት ነው ፤እንኳን ለውጭ ባለሃብት ቀርቶ ለሃገር ውስጥ ባለሃብትም እሚሰጥ አይደለም ፡፡ ኢትዮጲያ አየር መንገድን ከአውሮፕላኖቹና ከቁሳቁሶቹ ጋር ብቻ በመለየት ወደ ግል ማዛወር የሚቻል ሲሆን ወደ ግል የማዛወር ሂደቱ ከመጀመሩ በፊት በመላ ሃገሪቱ በርካታ የአውሮፕላን ማረፊያ ሜዳ ባለቤት የሆነው የኤርፖርቶች ድርጅት ተለይቶ መውጣት አለበት ፡፡   
አየር መንገዱ ወደ ግል ይዛወራል መባሉ አየር መንገዱን ያተጋው ይመስላል ፤ በዚህም መሰረት ፤ለረጅም ግዜ ያስራ ተቀምጠው የነበሩ በሞተር ችግር የማይሰሩ ሞተሮችን ማስነሳትና ወደ ስራ እንዲጀመር ማድረጉ ተዘግቧል ፡፡ ሪፖርተር ጋዜጣ እንደዘገበው ‹‹የኢትዮጵያ አየር መንገድ የሮልስ ሮይስ ሞተሮች የተገጣጠሙላቸው አራት ቦይንግ 787-8 አውሮፕላኖች ካለፈው ሚያዝያ ወር ጀምሮ ቆመው የነበሩ ቢሆንም፣ ከሞተር አምራቹ ኩባንያ ጋር በመነጋገር ሞተሮቹ እየተጠገኑ አውሮፕላኖቹ ወደ ሥራ በመመለስ ላይ እንዳሉ ሲገለፅ አየር መንገዱ ለቆሙት አውሮፕላኖች ካሳ እየተከፈለው መሆኑን ገልጿል››፡፡ የሁለቱ ድርጅቶች መቀላቀል ለሙስና ሰፊ በርን የከፈተ መሆኑ፤የር መንገዱ ግልጽ ባልሆነ መንገድ የገዛቸውን አውሮፕላኖችን መልሶ መሸጡ እንደገና መልሶ የሸጣቸውን አውሮፕላኖችን እንደሚከራይ ፤ የሰራተኛ አያያዙ ችግር እንዳለበት፤ እንዲሁም የስራ ቅጥርና ዝውውርን በተመለከተ የዘመዳማቾች ቤት ነው ተብሎ በሰፊው የሚተች ተቋም መሆኑ ይታወቃል ፡፡ 
የኢትዮጲያ መብራት ሃይል ቢሆን ባለፈው አመት ብቻ 128 ሚሊዮን ዶላር ለሃገሪቱ ያስገባ ሲሆን ይኀው ለጎረቤት ሃገራት መብራትን መሸጥ አትራፊና የውጭ ምንዛሬን የሚያስገኝ ሲሆን በሃገር ውስጥ የኤሌክትሪክ ስርጭትንና ማከፋፈልን ለማሻሻል ሲሆን የሃገር ውስጥም ሆነ የውጭ ባለሃብቶች ቢገቡበት የአገልግሎት አሰጣጡን የሚያሻሽለው ሲሆን ነገር ግን ወደ ውጭ የሚላከውና ለሀገሪቱ የውጭ ምንዛሬን የሚያስገኘው ዘርፍ ግን በመንግስት እጅ ሆኖ ቢቆይ የሚያስገኘው ጠቀሜታ መታየት አለበት፡፡ በእርግጥ ሃይልን በማሰራጨትና በማከፋፈል ላይ በግል ባለሃብቶች መግባታቸው እንደ ኢትዮጲያ ላለ ትልቅ ሃገር አስፈላጊ መሆኑን ጠ/ሚሩ ገልፀዋል፡፡ የተመረተ ሃይል እያለ ነገር ግን በስርጭትና በማከፋፈል ሂደት ሃይል በተደጋጋሚ እየተቆራረጠ መሆኑና በኢኮኖሚው ላይ በተለይም በማምረትና በከተሞች አካባቢ በአገልግሎት ዘርፍ ላይ ጉዳትን እያደረሰ መሆኑን መረዳት ይቻላል፡፡ ማንኛውም ሰው እንደሚገምተው የግል ባለሃብቶች  በመብራት ማከፋፈልም ሆነ ማሰራጨት ዘርፍ ሲሰማሩ አሁን ያለው ርካሽ የሃይል አቅርቦት አይኖርም ነገር ግን የሃይል መቆራረጡ ይቀንሳል ዋጋ ግን ወደድ ይላል ይህን ለህብረተሰቤ ግልፅ በማድረግ ይጠበቃል፤ በርካታ ትላልቅ የመንግስት ድርጅቶች ወደ ግል ወደ የተዛወሩባቸው ሃገራት የዋጋ መጨመር በስፋት ታይቷል፡፡
ኢትዮ ቴሌኮም ቀድሞ የመገናኛናት ትራንስፖርት ሚ/ር ጋር የተቀላቀለና በከተማው ውስጥ ያሉ የመንግስት ህንጻዎችንና ሰፋፊ መሬቶችን የያዘ ስለሆነ እነኚህን የሃገር ንብረቶችን ከቴሌኮሙ ቁሳቁሶች መለየትና ቴሌን ከነቁሳቁሱ ማዛወርና የሃገር ሃብት የሆኑት ህንጻዎችን ግን ወደ መንግስት ንብረትነት መቀላቀል ያስፈልጋል ፡፡ ይህ ብቻ አይደለም የድርጅቶቹን ሃብትና እዳ መግለጫ ለማዘጋጀት እንዲሁም በትክክል ድርጅቶቹ በገበያው ምን ያህል እንደሚያወጡ ‹ማርኬት ካፒታላይዜሽን› ምን ያህል እንደሆነ በገለልተኛ ኦዲተሮች ማዘጋጀት ራሱ እስከ አንድ አመት ድረስ ሊፈጅ የሚችል ነው፡፡
ከዚህም በተጨማሪ ወደ ግል የማዛወሩ ሂደት ለግዜው የሃገሪቱን የውጭ ምንዛሬ እጥረትን ለማቃለልና የገንዘብ እጥረትን ለማቃለል ቢረዳም ውሎ አድሮ ግን በሚገኘው ገቢ ሌላ አቅምን የሚፈጥር እንዲሆን ማድረግ ያሻል፡፡

dr abey change in Eprdf, ethiopia



‹‹በለውጥባቡሩያልተሳፈረኢህአዴግ ፤ የኢህአዴግአባልነኝማለትአይችልም››
ዶ/ር አቢይአህመድ
እስካሁን ድረስ ለውጡን በጠቅላይ ሚ/ር ዶ/ር አቢይ አህመድ ወደ ስልጣን መምጣትንተከትሎምበርካታበጎየለውጥጅምሮችንእያየንሲሆንለሃገሪቱናበተስፋመቁረጥውስጥበመሆንስደትንየሙጥኝብሎለነበረውለአዲሱትውልድተስፋንየሚያጭርነው፡፡በርካታነባርአመራሮችበትግሉዘመንጭምርየነበሩስልጣንበቃኝእያሉመሰናበታቸውይበልየሚያሰኝሲሆንከደህንነቱምከመከላከያውናእንዲሁምከፓርቲውጭምርጉምቱዎቹናበህዝብዘንድተወዳጅያልነበሩቱናበሙስናዋነኛተጠርጣሪየነበሩወንበሩንትተናልማለታቸውለብዙሃኑየሃገሬሰውመልካምዜናነው ምራትየለማቲምየሚባለውናኦህዴድውስጥየተፈጠረውቡድንበድፍረትወደመድረኩበመምጣትለውጡንየመራሲሆንብአዴንምየኦህዴድንያህልአይሁንበአማራክልልፕሬዝደንትበገዱአንዳርጋቸውየሚመራውብአዴንቡድንምበክልሉህዝብዘንድድጋፍንያገኘሲሆንየለውጡንአስፈላጊነትየተረዳሲሆንደህዴንምውሎአድሮየለውጥሂደቱንመቀላቀሉአይቀርም ፡፡ለውጡንመደገፋቸውበጥርጣሬሲታዩየነበሩትና ፤ከለውጡባቡርእየተንጠባጠቡያሉትየቀድሞአመራሮችመካከልየደኢህዴንዋና ሊ/መንበርየነበሩትአቶሽፈራውሽጉጤናምክትላቸውከሊቀመንበርነታቸውመልቀቃቸውለዚህጠቋሚነው ፡፡በአንጻሩመጀመሪያበመሪነትኦህዴድቀጥሎምበድፍረትየለውጡአካልሆነውሆነውተገኝተዋልየብአዴንአመራሮችበባህርዳሩህዝባዊሰልፍያደረጉትንግግርለዚህማሳያነው ፡፡
አቶ ለማ መገርሳ ‹‹የለውጡን ሂደት በመደገፍ የኢትዮጲያን ህዳሴ እናስቀጥል ›› ሲሉ በህወሃት በኩል  ግን እስካሁን ድረስ የለውጡ አካል ነኝ ሲል አልተሰማም ፡ አመራሮቹም ሆነ ሚዲያዎቹ ለውጠን እንደግፋለንሲሉ አልተሰማም ይህ ነገር በጤና ነው ወይ ብለው አንዳንድ ሰዎች ይጥይቃሉ ፡፡ ህወሃት ቀድሞም ሁሉም ካልተሰጠኝ በሚል አኩራነቱ የሚታወቅ ድርጅት ሲሆን በአቶ መለስም ዘመን ቢሆን በፌደራል መንግስቱ ለድርጅቴ ተገቢው ስልጣን ውክልና አልተሰጠውም በሚል ተወካይ ላኩ ሲባል ተወካይ አልክም በማለት አቶ መለስንም ጭንቅላታቸውን ሲያዞር የነበረ ድርጅት ነው ፡፡ አንዳንድ የቀድሞ የፌደራል አመራሮችም የቀድሞውን የኢንሳ ስራ አስኪያጅ የነበሩት ዶ/ር ተክለብርሃን ጭምር በዶ/ ር አቢይ የለውጥ እንቅስቃሴ ጥርጣያቸውን በሚዲያ ሲገልፁ ተሰምቷል፡፡
ይህ ጉዳይ ማለትም ኢኤንንና ቲቪ ትግራይ ያሉ ሚዲያዎች የሰኔ 16ቱን ድጋፍ ሰልፍ አለመዘገባቸው ኢኤንን የተባለውን ቲቪ ጣቢያ እስከመዘጋት ያደረሰ ከባድ ዋጋን አስከፍሏል፡፡ የህወሃት የለውጡን ከልብ አለመደገፍ አንድም ከፌደራል መንግስቱ ጉዳዮች ራሱን እያገለለ እንዲሄድ ሲያደርግ ደኢህዴን ጭምር አመራሮቹን በመለወጥ የለውጥ ሂደቱ ተሳታፊ እየሆነ ባለበት ሁኔታ ወይ እንደሌሎቹ የአመራር ለውጥ ማድረግ አለበት ፤ አለበለዝያ ግን ከፌደራል መንግስቱ የተለየ አቋምን መያዝ በረጅም ግዜ ለድርጅቱ አዋጭ መሆኑ አጠራጣሪ ነው ፡፡ 
በጠቅላይሚኒስትሩአበረታችየለውጥእንቅስቃሴበመነሳትከወደአሜሪካወደኢትዮጲያየውጭምንዛሬእንዳይገባ ሲደረግ የነበረው ዘመቻ መቆሙ በዜና ማሰራጫዎችተሰምቷል፡፡ ከዚህም በላይእነዳንኤልብርሃነናአላመራውየተባለውየኢኤንኤንጋዜጠኛውድሮስግንቦት 7 ጥይትተኩሶያውቃልእንዴ?››ቢሉምግንቦት 7 የትጥቅትግሉንማቆሙንምአስታውቋል ፡፡በውጭያሉኢትዮጲያውያንም‹‹ለዛፉናለግድግዳውእስኪገርመውድረስ››በተቃውሞሲናወጡየነበሩኢምባሲዎችደጃፎችአሁንበድጋፍሰልፍተጨናንቀዋል፡፡በባህርዳርየተካሄደውደማቅናታላቅህዝባዊሰልፍለጠ/ሚሩናለለውጥሃይሎችከፍተኛየሞራልስንቅእንደሚሆንይጠበቃል ፡፡ጠ/ሚሩከወጣቱዘንድያገኙትድጋፍከፍተኛሲሆንበአመፅተወጥሮለነበረውኢህአዴግምጭምርየመተንፈሻግዜንሰጥቶታል፡፡ይህንንፋታገዢውፓርቲውስጥያሉለውጥንየማይፈልጉሃይላትመልሰውእሚጠናከሩበትናከእጃቸውየወጣውንስልጣንበመልሰውበማስገባትእሚነሳሳሱበትናጊዜየሚገዙበትእንዳይሆንከጠ/ሚሩናበዙሪያቸውካሉቅንአመራሮችመዘናጋትንማስወገድያሻል፡፡
ነገርግንይህንለውጥወደኋላእንዳይመለስናእንዲቀጥልየሚፈልገውህዝብእጅግብዙሲሆንጠቅላይሚኒስትሩምወደኋላእንዳይመለስየማድረግተግባርይጠብቃቸዋል፡፡በቅርቡበአፋርሰመራተገኝተውባደረጉትንግግር‹‹የጀመርነውንነገርወደኋላየሚቀለብንስማንኛውምነገርለመሸከምዝግጁአይደለንም፤ ኢህአዴግውስጥለውጥመጥቷል፤ ተሃድሶመጥቷል ፤ 90  በመቶበላይአባልየለውጥጉዞውስጥገብቶየገባነውንቃልለመተግበርህዝባችንንይቅርታጠይቀን ፤ መካስአለብንበሚልእየተንቀሳቀስንነው…ቀድሞየነበረውጭንቀትእንዳይመለስየሚከፈለውዋጋይከፈላል…..የኢትዮጲያህልውናአደጋውስጥየሚያስገባሰላምየሚያሳጣንናጭንቀትውስጥየሚከተንሰላምየሚነሳንናእናቶችልጆቻቸውወጥተውቤትእስከሚገቡድረስእሚጨነቁባትኢትዮጲያዳግምእንዳትመለስዋጋይከፈላል፤ ጠንክረንእንወጣለንብለንተስፋእናደርጋለን››ሲሉእንዲሁም‹‹በለውጥባቡሩያልተሳፈረየኢህአዴግአባልነኝማለትአይችልም….90 በመቶየሚሆነውየኢህአዴግአባልምበለውጡባቡርየተሳፈረመሆኑን››አረጋግጠዋል ም/ጠ/ሚርደመቀመኮንንበበኩላቸውበባህርዳሩሰልፍላይሲናገሩለውጡ‹‹ወደኋላመመለስንሳይሆንማዝገምንአይታገስም…ለውጡበማይቀለበስበትደረጃደርሷልበፍጥነትእንስተካከላለን››ብለዋል፡፡
ይሁንናሁሉምየኢህአዴግአባላቶችበተለይምበቀደመውዘመንያሻቸውንያደርጉ ፤ እንዲሁምተጠቃሚየነበሩናበሙስናውየተነካኩቱበቀላሉየአዲሱን ጠ/ሚ/ር አስተዳደርይቀበላሉማለትአስቸጋሪነው ፡፡ጠ/ሚሩበርካታፈተናዎችንመወጣትየሚጠብቃቸውሲሆንድርጅታቸውአባላትይህንንየለውጥሂደትየማይደግፉትከሆነስራቸውንያከብድባቸዋልለምሳሌበየአካባቢውበተፈጠረግጭትየተፈናቀሉኢትዮጲያውንበሚሊዮንየሚቆጠሩመሆናቸውንየዓለምዓቀፍናየሃገራችንየሰብአዊተቆርቋሪድርጅቶችበሃገርውስጥበርካታዜጎቻቸውከተፈናቀሉባቸውየኣለምሃገራትአንዷሃገራችንመሆኗንአስታውቀውሚዲያዎችምይህንንበሰፊውዘግበዋል፡፡ ዶ/ር አቢይከተመረጡወዲህኢህአዴግሁለተኛዙርድርጅታዊማጥራትየሚጠብቀውይመስላል፤ በዚህምለውጡንያልደገፉትተለይተውየሚታወቁበትይሆናል፡፡
ለውጡየሰዎችናየአመራሮችብቻሳይሆንየህግጋትማሻሻያናለውጦችንይጨምራል ፤ ይሁንናግንአሁንምድረስመለቀቅየነበረባውሰዎችእንዳልተለቀቁ፤ እንዲሁምበቂሊንጦናበሌሎችማረሚያቤትየሚገኙእስረኞችበቃሊቲእስርቤትውስጥጨምሮከፍተኛድብደባእንደተፈፀመባቸውእንደሚገኙኢቢሲንጨምሮየተለያዩሚዲያዎችእየዘገቡየሚገኙሲሆንይህየፍትህስርአትበፍጥነትመስተካከልእንዳለበትናየህግማሻሻያዎችንጨምሮበተለይምአፋኝየሆኑትየሸብርህጉናየመንግስታዊያልሆኑድርጅቶች ፤ የፕሬስህጉበፍጥነትእንዲሻሻሉናየፍትህስርአቱመልሶ እንዲዋቀርየሰብአዊመብትድርጅቶችእየጎተጎቱሲሆንየህግንክፍተትእያወቁበመጠቀምየቀደሙትአስተዳሮችአገዛዛችንንያጠነክርልናልቢሉምጭራሽበመንግስትላይያለውአመኔታእንዲሸረሽርበማድረግስርአቶቹንአዳክሟልእንጂውሎአድሮአልጠቀማቸውም ፡፡የእነኚህህጎችመሻሻልየተሰደዱጋዜጠኞችወደሃገርቤትእንዲመለሱ፤ እናየሰብአዊመብትእንዲከበርበእጅጉየሚረዳስለሆነ ጠ/ሚሩህጎቹንለማሻሻልቅድሚያመስጠትይገባቸዋል፡፡ጠ/ሚሩለፍትህስርአቱየሚያሻሽልአንድኮሚሽንመቋቋሙናስራመጀመሩየተገለፀሲሆንጉዳዩግንፍጥነትንየሚጠይቅበመሆኑቅድሚያየሚሰጣቸውንህግጋትንበቶሎማሻሻልእንደሚገባየሰብዓዊመብትድርጅቶችእያሳሰቡይገኛሉ ፡፡ አስገራሚውነገርኢህአዴግምሆነደርግክፉኛየሚተቿቸውንጉሰነገስቱያወጧቸውንህግጋትከዋነውየወንጀለኛመቅጫህጉንከማሻሻልበስተቀርክፍተቶችያሉበትንየወንጀለኛመቅጫስነስርአትህጉንሳያሻሽሉሲሰሩባቸውየቆዩናአሁንምእየተሰራበትያለውየፍትሃብሄርህጉናየወንጀለኛመቅጫየስነስርአትህግጋትተጠቃሾችናቸው፤ እንዲሁምአስፈላጊናአንገብጋቢየሆኑህግጋትምሳይወጡሰፊየህግክፍተትበመፈጠሩምክንያትለሙስናናለመልካምአስተዳደርመታጣትመንስኤሆኗል፡፡የህግማሻሻያዎችንማድረግይዋልይደርየማይባልናጠ/ሚሩበህግተመስርተውእንዲሰሩናየህዝብንጥያቄበተለይምየመልካምአስተዳደርችግርንበቶሎእንዲመልሱ ፤እንዲሁምለውጥንየሚቃወሙየውስጥሃይሎችንበተግባርለማሳመንናተጨማሪየህዝብድጋፍንለማግኘትያስችላቸዋል ፡፡
ራሳቸው ዶ/ር አቢይለፓርላማውባቀረቡትሪፖርትመሰረት ‹‹የማሰርእንጂ፤የመፍታትህግየለንም›› ሲሉእውነቱንተናግረዋል ፤ በወንጀለኛመቅጫህጉመሰረትአንድሰውከተፈረደበትወንጀልነጻሆኖቢገኝእንኳንያላጠፋውንጥፋትጥፋተኛነኝብሎይቅርታጠይቆሊፈታይችልይሆናልእንጂቅጣቱንሳይጨርስከእስርቤትሊወጣአይችልም፤ የዳኝነትስርአቱየዳኝነትክለሳየማያደርግናበስህተትየተሰጠንፍርድደግሞየሚያይበትአሰራርየሌለውመሆኑነው ፡፡
ከዚህበመነሳትአፋኝየሆኑህግጋት ፤ እንዲሁምበአጠቃላይየፍትህስርአቱበጃንሆይግዜ በ50ዎቹ ከወጣውናበርካታክፍተቶችካሉበትከወንጀለኛመቅጫስነስርአቱጀምሮከዛሬነገይሻላልቢባልምበአቶሃይለማርያምግዜይሻሻላልቢባልምሳይሻሻልቆይቷል፤ የንግድህጉምበንግድምክርቤቶችይሻሻላልበሚልበጉጉትይጠበቅየነበረቢሆንምሳይሻሻልቀርቷልየፍትህስርአቱበህግክፍተትብቻሳይሆንእስከማረሚያቤትየእስረኞችአያያዝ ፤ የአቃቤህግክስአመሰራረት ፤ ይቅርታናምህረትአሰጣጥናበህግአተረጓጎምድረስሰፊየህግክፍተትእንዲፈጠርያደረጉትእነኚሑየወንጀለኛመቅጫየስነስርአትህግ፤የሽብርህጉናሌሎችምየተዛቡህግጋትመሆናቸውንበርካታየህግባለሙያዎችእየተናገሩይገኛሉ ፡፡ የምህረትአዋጅበፍጥነትመፅደቁመልካምሲሆንነገርግንበህብረተሰቡከዛሬነገይሻሻላሉበሚልየሚጠበቁትንከላይየተጠቀሱትንጊዜሳይሰጡማሻሻልተገቢነው፡፡