Thursday, August 15, 2013

የመንፈስ ህልውና


በሚሊየን አመታት ውጥ የሰው ዘር ራሱ ህልውናውን ሊያጣ ይችላል ። በዚህ ምድር ላይ የምናየው ነገር በጊዜ ውስጥ ሊፈራርስና ሊጠፋ እንደሚችል መገመት ይቻላል ።
በምእራባውያን የስልጣኔ አስተሳሰብ መሰረት ስልጣኔ ከተጀመረ ቢበዛ አስር ሺህ አመታት አይበልጥም ። የምስራቁ ቅድመ-ታሪክ የሚባለውን የሚያጠቃልል ሲሆን በአንፃሩ የምእራበውባውያን ስልጣነቤ ኔም ሆነ አስተሳሰብ ከዘመናዊው ውምን ወይንም በስነ-ሰብ «አንትሮፖሎጂስቶች» ተመራማሪዎች  ከተደረሰበት የምርምር ውጤት አያልፍም ። ይህም ማለት በአብዛኛው የሰው ልጅ እርሻን ጀምሮ የቤት እንሰሳትን አርብቶ መኖር ከጀመረበት ዘመን የሚጀምር ነው ። ነገር ግን ቅድመ-ታሪክ ከዚያም ያለፈ ሲሆን በመቶ ሺዎች አመታት የሚ ቆጠር እድሜን ያስቆጠረ ነው ።  
መንፈስን በተመለከተ አይሁዳውያን ፣ ኢራናውያን (ፐርሺያኖች) እና አረቦች እና ህንዶችናቸው ሊቃውንቱ ። በአብዛኛው ምእራባውያን ቁሳዊ ነገርን በመፍጠር ረገድ ተወዳዳሪ የላቸውም ። ምእራባውያና ባሏቸው ወፈ - ሰማይ ኩባንያዎቻቸውና ኮርፖሬሽኖቻቸው አማካይነት በአለም ላይ ግዙፍ ምጣኔ-ሐብት እንቅስቃሴ ባለቤቶች ሲሆኑ በአንፃሩ መንፈሳዊ ነገርን በተመለከተ ግን ከምስራቅ ሰዎች ብዙ የሚማሩት ነገር አለ  
በአንፃሩ ቁሳዊ ነገርን በመፍጠር ረገድ ግን ምስራቆቹ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ከምእራባውያን በመማር ምጣኔ-ሀብታቸውን ማሳደግ እና በኢንዱስትሪ መበልፀግ የጀመሩት አሁን በቅርብ ነው ማለት ይቻላል ። ለዚህም በአንድ በኩል ቀድመው በሳይንስና ቴክኖሎጂ የበለፀጉት ምእራባውያን ቀድሞ አፍሪካውያንን በባርነት ፣ በኋላም አፍሪካንና እስያን በቅኝ ግዛት በመ  ግዛት ለመቶዎች አመታት ወደ ኋላ እንዳያድጉ ማነቆ ስለሆኗቸው ሲሆን ፣ በኋላ ላይም ቢሆን እነኚህ በምእራባውያን አጠራር «ሶስተኛው ዓለም» በመባል ሲጠሩ የነበሩት መጀመሪያ ለይ ላይ የአገሮቻቸውን አስተዳደሮች ከቅኝ ገዢዎች በተረከቡባቸው ወቅቶች ካለማወቅና ብሄራዊ ስሜታቸውን ለማነቃቃት በአንዛኛው ትክክለኛውን የእድገትና የልማት ጎዳናን ሳይከተሉ በመቅረታቸው ምክንያት ከምእራባውያን አይነት የዳበረ እድገትን ለአስርት አመታት መፍጠር አቅቷቸው ቆይተዋል ።
ሀያልና ግዙፍ ኢኮኖሚን በሀያና በሰላሳ አመታት ውስጥ የገነባችና ቻይናን  ብንወስድ ቻይና በማኦ የአገዛዝ ዘመን በባህል አብዮት እድገት ገጠር ነው ያለከው በሚል የተማረውን ሀይሏን ወደ ገጠር በመላክ በሚሊዮን ዜጎቿን ለእልቂት ስትዳርግ ምጣኔ ሀብቷም የሶስተኛው አለም ከሚባሉት ሆኖ ቀርቶ ቆይቷል ። ቻይና ከማኦ ህልፍት በኋላ በዴንግ ዚያዎ ፔንግ ዘመን «ድመቷ ጥቁት ወይም በነጭ መሆኗ ሳይሆን ፣ ድመት መያዝ መቻሏ ነው» በሚል አለመካከት ካፒታሊዝምም ሆነ ሶሻሊዝም ዋናው ምጣኔ ሀብቱን ማሳደጉና የህዝብን የኢኮኖሚ ጥያቄን መመለሱ ነው በሚል ተግባራዊ «ፕራግማቲክ» በሆነ አስተሳሰብ ወደ ካፒታሊዝም የኢኮኖሞ ስርአት በመግባት ምእራባውያን ለመድረስ በርካታ መቶ አመታት የፈጀባቸውን በሀያና ሰላሳ አመታት ውስጥ ማሳካሰት የቻለችው ። ቀድሞ ታዳጊ ይባሉ የነበሩት አገራት ወደ ቁሳዊ እድገት ፈጠራ ከገቡ ምእተራባውያንን በቀላሉ ማለፍ እንደሚችሉ ቻይናና ሌሎቹንም ተመሳሳይ የእድገት ጎዳና  ውስጥ የገቡት «ብሪክስ» በመባል የሚታወቁት አገራት አይነተኛ ምስክሮች ናቸው ።      
ብላስቶቭስኪ የተባለችው የአዲሱ ዘመን እንቅስቃሴ መስራች ራሺያዊት እንደምትለው ምእራባውያን ለህንዳውያን መፋንፈሳውያን የበላይነትን መቀለበል አለባቸው ።
በነገራችን ላይ አፍሪካውያንና እስያውያን ከተፈጥሮ ጋር ያላቸው ትስስር እጅግ ጠንካራ ነው ። ለምሳሌ በቻይና አንድ ቤሄረሰብ አንድ ልጅ ሲወለድ አንድ ዛፍ የተ ይተከልለታል ፣ ልክ ያ ሰው ሲሞት ሲወለድ የተተከለለት ዛፍ ተቆርጦ የአስከሬን ሳጥን ይሰራበትና ይቀበርበታል ። ዛፉም ለዛ ሰው የተተከለ እንደመሆኑ ማንም ሰው አይቆርጠውም ። ለደኑ በየጊዜው የአምልኮ ስርአትን የሚያደርጉለት ሲሆን አካባቢውም በደንና በጫካ የተሸፈነ ሲሆን ደናማው አካባቢ በመባል በቻይና ይጠራል ። አፍሪካውያንም ተፈጥሮን የማይነኩ ሲሆኑ ከሚበሉትና ከሚጠጡት ውጪ ደኑን የማይነኩትና ጉዳትን የነማያደርሱበት ሲሆን ጥቅጥቅ ካለው ደን ጋር ጎን ለጎን በሰላም ለዘመናት ሲኖሩ ቆይተዋል ። በአማዞንም ደኖችም ውስጥ እንዲሁ ጥንታዊና ቀደምት የሆኑት የአማዞን ነዋሪዎች ከተፈጥሮ ጋር ለሺዎች አመታት በሰላምና ተፈጥሮውን ሳይነኩት ኖረዋል ።
አንድ ሰው እነኚህን ሰዎች ባእድ አምላኪዎች ናቸው ሊል ይችላል ፣ ነገር ግን ከተፈጥሮ ጋር ተግባብተው ለሺዎች አመታት መኖር መቻላቸውን ማየት ይገባል ። በአሁኑ  ዘመን ሳይንስና ቴክኖሎጂ ባደገ ቁጥር በተፈጥሮ ላይ የሚደርሰው ጉዳትም እያየለ ሲሄድ በተለያዩ አገራት የሙቀት መጨመር ፣ የጎርፍ መጥለቅለቅ ፣ የዓለም ሙቀት መጨመር ፣ የአካባቢ መጎዳት ፣ የአፈር አሲዳማ መሆን ፣ የአሲዳማ ዝናብ መጣል፣የውቅያኖስና የውሀ አካላት መጠን መጨመርና በሰሜንና በደቡብ ዋልታዎችና በተራራዎች አናት ላይ ያለ በረዶ መቅለጥ እየታየ ነው ። ይህም ዘመናዊው ሰው በእውቀቱ ተፈጥሮን በመቃረኑ የተከተለ መሆኑ አያሻማም ። የሰው ልጅ በገዛ ራሱ አስቦና ተጨንቆ የፈጠረው እውቀቱ ጠላቱ ሊሆን እንደሚችል ለመረዳት በአካባቢ ላይ የሚደርሰውን ጉዳት በማየት በቀላሉ መረዳት ይቻላል ።    
         

ሄግል


ሱን ሱ የተባለው ጥንታዊ የቻይና ፈላስፋ የሰዎች ክፋት የሚወገደው በትምህርት ነው ይላል ። በምእራቡ አለም ታዋቂ አርቲስቶች በአንድ በኩል በንግድ በቢዝነስ ፣ በሌላ በኩል ደግሞ ለረጅም ጊዜ የሚቆዩ ስራዎችን ነው እሚሰሩት ። ይህም በአንድ በኩል ለረጅም ጊዜ የሚቆይ (Timeless) የሆነ ስራን እሚሰሩ አርቲስቶች ረጅም ጊዜ የሚቆይን ስራን ሊሰሩ እድል ያገኛሉ ። ነገር ግን ለንግድ ወይም ለገቢ ብቻ ብለው ስራን እሚሰሩ ግን ስራቸው የአንድ ሰሞን ብቻ ሆኖ ይቀራል ።
የማስታወቂያ ስታዎችን ብንወስድ በእኛ ሀገር በአርቲስቶች የሚሰራ ሲሆን በሌላው አለም ግን በሰለጠኑ የገበያ ባለሙያዎች ነው እሚሰራው ።
አራቱ እውቀት እሚሰበሰብባቸው መንገዶች ምልከታ (Observation) ፣ ነገሮችን የማየትና የመረዳት ችሎታ፣ የማሰብ ችሎታ ፣ እርግጥ የማስታወስ ችሎታ በላይ የማሰብ ችሎታ የበለጠ ነው ። ማንም ሰው ሊያስታውስ ቢችልም ያንን ነገር በተለየ መንገድ የማሰብ ችሎታ ግን የተለመደ አይደለም ። በአለም ላይ የምናያቸው በርካታ ታላላቅ ነገሮች የተፈጠሩት የማሰብ ችሎታ ባላቸው ሰዎች ሲሆን ።
የማስታወስ ችሎታ፣ ትምህርትና ብዙ ማንበብ ፣ ሲሆኑ እነኚህ ሁሉ ነገሮች ቢኖሩም ለአንድ ሰው ስኬታማ እንዲሆን ትጋት (ዲሲፕሊን) መሰረት ነው ። ሶስቱ ምልከታ «ኦብዘርቬሽን» ሙከራ «ኤክስፐርመንቴሽን» እና እነ ኒውተን እና ሌሎች የአብርሆት ዘመን ፈላስፎች የዘገቡት

የወንዶች ዓለም ክፍል -2


በብዙ እንሰሳት ውስጥ የወንዱ ቦታ ጎላ ሊል ይችላል ። በአንበሳ ብንመለከት ዋናውን አደን  የምታከናውነው ሴቷ አንበሳ ስትሆን ፣ በአንፃሩ ወንዱ አንበሳ ብዙውን ጊዜ አያድንም ። ሴቷ አንባሳ  የሚያስቸግር ነገር ሲመጣ ካልሆነ በስተቀር ወንዱ ብዙም በአደን አይሳተፍም ። ይሁን እንጂ አንድ አነስተኛ የአንበሳ መንጋ የሚመራውም ሆነ ጥበቃ የሚደረግለት በወንዱ አንበሳ አማካይነት ነው ። ይሁን እንጂ ይህ በአንበሶች ዘንድ «የፖለቲካ» ችግር የለም ።
ሜሪቶክራሲ ከሴቷ ይልቅ የወንዱን የበላይነትን የሚያጠናክር ነው ። በአብዛኛው ሜሪቶክራሲ ውስጥ መወዳደር የሚችለው የተሻለ የመወዳደር አቅምን የሚሰጠው ለወንዱ ነው ። ይህም አንዱ በወንዱና በሴቷ መሀከል የበዛ የሰፋ  ልዩነት እንዲፈጠር ካደረጉት ነገሮች አንዱ ይሄው ነው ።
አንዳንድ ዘርፎች በአብዛኛው በወንዶች ብቻ የተያዙ አሉ ። ለምሳሌ የሲልከን ቫሊ ፣ ዎል ስትሪትና ብንመለከት በአብዛኛው ወንዶች ናቸው ። እንዲሁም ፊፋን ብንወስድ ፊፋ «የወንዶች ክበብ» ነው ይባላል ።
እንደ ስካንዴበኒቪያና አንዳንድ የእስያ ሀገራት ሴቶች በአንፃራዊነት ከወንዱ ጋር የሚመጣጠን ስፍራን ይዘው ይገኛሉ ። በአብዛኛው ለሴቶች ከወንዱ ይልቅ አለማደግ ምክንያቱ በስራቸውና በቤተሰባቸው መሀከል አመጣጥኖ መጓዝ መቻል ለብዙ ሴቶች  ፈተና እንደሆነ ብዙ ተመራማሪዎች የደረሱበት ጊዳይ ነው ።

ምጣኔ-ሐብት ማዘመን



የንግድ ስርአቱን ማዘመን
በሀገራችን ያለ የንግድ ስርአት ዘመናዊ መሆንና ይበልጥ በገበያው አንፃር መቃኘት መቻል ይኖርበታል ። በአሁኑ ወቅት ያከው ለው የንግድ ስርአት አንድ ነጋዴ ወይንም የተወሰኑ ነጋዴዎች ተሰብስበው ገበያውን ለተወሰነ ጊዜ የዋጋ ግሽበትን ሊያስከትሉበት ይችላሉ ። ነገር ግን ዘላቂ የሆነ የዋጋ ግሽበትን ሊያስከትሉ እንደማይችሉ ግን ግልፅ ነው ። በአንድ ወቅት ገበያ ላይ ያለውን ጨው ከገበያ በማስወጣትና በመደበቅ የጨው ዋጋ ሶስትና አራት እጥፍ ሊያድግ መቻሉና ገበያ ትርምስን መፍጠሩ የሚታወስ ነው ።
የንግድ ስርአቱ ዘመናዊ አለመሆኑና አንድ ደርዝ አለመያዙ ለመንግስትም ቢሆን ንግዱን በሚፈልገው የፖሊሲ አቅጣጫ ለመምራት እንዳላስቻለው ግልፅ ነው ። የንግድ ስርአቱ ሰንሰለት መርዘም ፣ መሀል ላይ የደላላ መግባት አንዲሁም የትራንስፖርት ዋጋው መናር ፣ እንዲሁም አግባብ የሆኑና ዘመናዊ የሆኑ የማቀዝቀዣና የማስቀመጫ ፣ የተመረተው የግብርና ምርት ሳይበላሽ ለገበያው የሚቀርብበት የተፋጠነ መንገድ አለመኖር ፣ በምርት ወቅት የሚደርስ ብክነት ከውጭ ከመጣው የዋጋ ንረት በተጨማሪ በሀገራችን ላለው የምግብ ዋጋ እየናረ መሄድ ዋነኛ ውስጣዊ ምክንያቶች ናቸው ።
    በዚህም የመሰረታዊ ሸቀጦች አቅርቦት መሰናከሉ ያሳሰበው መንግስት አለም አቀፍ ቸርቻሪዎችንና ትላልቅ ሱፐር ማርኬቶችን ለማስገባት እስከ ማሰብ ደርሷል ። በነገራችን ላየጥ  ይ ህንድ በሀገሯ ተመሳሳይ የዋጋ ንረትና የአቅርቦት እጥረት ስላጋጠማት ዓለም አቀፍ ሱፐር ማርኬችን በሀገሯ እንዲሰሩ ለመፍቀድ ተገዳለች ። ተቃውሞ ቢገጥመውም የህንድ መንግስት ግን ፖሊሲውን ተግባራዊ በማድረግ ለሸማቿቾቹ የተሻለ አማራጭን ለማቅረብ ችሏል ። ዘርፉ ዋነኛ አትራፊ አንደመሆኑ የውጭ ባለሀብቶች በዚህ ዘርፍ እንዲገቡ የአገር ውስጥ ቸርቻሪዎች  ደስተኛ እንደማይሆኑ ግልፅ ነው ።
የውጭዎቹ አቅራቢዎች ትላለቅ እንደመሆናቸው አነስ ባለ ዋጋ ፣ እንዲሁም ከአለም ገበያ በሚገዙበት ወቅት አነስ ባለ ዋጋ ስለሚገዙ የተሻለ የዋጋ ቅናሽን ለሸማቹ ሊያቀርቡ ይችላሉ የሚል  ግንዛቤ አለ 
   
የአክስዮንና የካፒታል ገበያዎችን መክፍት
ሀገራችን የአክስዮን ገበያ በሀይለስላሴ ስርአት የነበረ ቢሆን «ካፒታሊዝም ሊያቆጠቁጥ ሲል ደረስኩበት» በሚለው የደርግ ዘመን እንደ ሌሎቹ የግል የአክስዮን ኩባንያዎች በመወረሱ ምክንያት ገበያው የለም ። ነገር ግን በአሁኑ  ወቅት ምጣኔ-ሀብቱ እደያደገ ባለበት ሁኔታ የአክስዮን ገበያ ቢኖር በአንድ በኩል ኩባንያዎች አዳዲስ ኢንቨስትመንትን ለማካሄድ ፣ የሚፈልጉትን ካፒታል በቀላሉ ከገበያው ማሰባሰብ ያስችላቸዋል ፣ በሌላ በኩል ደግሞ የአክስዮን ገበያውን እንቅስቃሴ በማየት የምጣኔ-ሀብቱን እንቅስቃሴ መቆጣጠርና መመልከት ይቻላል ። በምእራቡ ዓለም የአክስዮን ገበያው ጥሩ አእንቅስቃሴ ላይ ካለ የኢኮኖሚውን ጤነኛነት ሲያሳይ በአንፃሩ አክስዮን ገበያው መውደቅ ኢኮኖሚው ውስጥ ያለውን ችግር ለመንግስትም ሆነ ለመዋእለ-ንዋይ አፍሳሾች ይጠቁማል ።
ከዚህም በተጨማሪ የውጭ ባለሀብቶች በቀላሉ መዋእለ-ንዋያቸውን በአክስዮን ገበያው አማክነት የሚፈልጉትን ኩባንያ አክስዮኖችን በመግዛት ወደ ሀገሪቱ ኢንቨስት ማድረግ ያስችላቸዋል ። የአክስዮን ገበያ በአውሮፓ እንኳን ከተጀመረ ለምሳሌ በኔዘርላንድ በ17ኛው ክፍለ ዘመን የተጀመረና በጣም ረጅም እድሜን ያስቆጠረና የሀገራትን ኢኮኖሚ ሀይል እየሰጠ የሚያሞቅና እድገትን የሚያፋጥን ነው ።
የውጭ ኢንቨስትመንቱን የማፋጠን ሚናንም ሊጫወት ይችላል ። ይህም በተዘዋዋሪ መንገድ ኢኮኖሚውን ለውጭ ይበልጥ ክፍት ማድረግ ማለት ነው ይህን አንድን ኢኮኖሚ ለው ጭ ክፍት ሲያደርገው ከውጭ የሚፈጠር መልካምም ሆነ ጥሩ አጋጣሚ የራሱ ተፅእኖ እንዲጨምር ማድረጉ የማይቀር መሆኑ ግልፅ ነው ። ይህንም የውጭ ምንዛሬ እጥረት ላለባትና የውጭ መዋእለ - ንዋይ በበቂ ሁኔታ እየገባ ያለባት ሀገር በሆነችው ሀገር እጥረት በበቂ ሁኔታ ላልገባባት ኢትዮጲያ የአክስዮን ገበያ መክፈቱ ለውጭ መዋእለ-ንዋይ መፍሰስና ለውጭ ምንዛሬ ለማግኘት የተሻለ አቅምን የሚፈጥር ነው ።  
የውጭ ኢንቨስተሮች በአንድ ጊዜ ገንዘባቸውን በሚያወጡበት ወቅት -  ክፍት ማድረጉ ከውጪ ለሚመጡ የኢኮኖሚ ቀውሶች የመጋለጥ እድልን የሚያሰፋ ቢሆንም የቀውስ ዘመናት  አጭር እንደመሆናቸው ዘግቶ ከመቀመጥ ክፍት አድርጎ ከአለም አቀፍ ብለፅግና መጋራት የተሻለ ነው ።         
ኢ-ኮሜርስን (E-Commerce) እና የዘመናዊ ክፍያ ስርአትን ማዘመን
በሀገራችን ያለው የየክፍያ ስርአት ገንዘብን ፣ ቼክንና የክፍያ ማሽንን «ኤቲኤምን » የሚጠቀም ነው ። ነገር ግን እስካሁን ድረስ የክፍያ ስርአቱ ወደ ክሬዲት ካርድ (Credit Card) እና ዴቢት ካርድ ደረጃ አልደረሰም ። በዚህም ምክንያት በሀገራችን የኢ-ኮሜርስ (E-Commerce) እሚባል ነገር የለም - የክፍያ ስርአቱ ባለመኖሩ ምክንያት ነው ።
የድረ-ገፅ መገበያየት ደረጃ ባንደርስም ነገር ግን ወደዛ የሚደረገውን ሽግግር ለማጠናከር የሚሰሩ ስራዎችን ከአሁኑ መስራትና ቀስ በቀስ በድረ - ገፅ አማካይነት ግብይቶችን በማካሄድ በአንድ በኩል በሀገር ውስጥ የቀለለ የግብይት ስርአትን መፍጠር ሲቻል ከውጭ ሀገር ሆኖ ወደ ሀገር ቤት ማንኛውንም ነገር መግዛት ለሚፈልግ በቀላሉ ካለበት ሀገር ሆኖ ግዢን በመፈፀም ለሀገሪቱ ተጨማሪ ውጭ የውጭ ምንዛሬን ማስገኘት ይቻላል ።
ለዚህም ተአማኒ የሆነ ስርአትን በመዘርጋት ለገዢም ሆነ ለሻጭም ሁለቱም የሚተማመኑበት የግብይት ስርአትን ለመፍጠር ህጎችን ማውጣትና አስፈላጊ የሆኑ የግልና የመንግስት ተቋማትን መፍጠርን ይጠይቃል ።
በአሁኑ ወቅት ምሳሌ ብንወስድ መፅሀፍት ገበያ በአብዛኛው የሚከናወነው በድረ - ገፅ አማካይነት ሲሆን እንደ አማዞን ያሉ ድረ-ገፆች አማካይነት በአለም ላይ አንድ ሰው የዱቤ «ክሬዲት» ካርድ እስካለው ድረስ የሚፈልገውን መፅሀፍ ማዘዝና መግዛት ይችላል ። ይህም በመሆኑ ንግዱ እጅግ የተሳካ በመሆኑ ምክንያት በተለያዩ የምእራብ ሀገራት ባሉ ዋና ዋና ከተሞች ውስጥ በርካታ የመፅሀፍ መሸጫ ሱቆች እየተዘጉ ሲሆን ፣ የሱቆቹ መዘጋት መልካም ነው ለማለት ሳይሆን ኢ-ኮሜርስ ምን ያህል ሀይልና አቅም እንዳቀለው ለማሳየት ነው ። ኢ-ኮሜርስ (E-Commerce) ለሀያ አራት ሰአታት የሚሰራ ሲሆን አንድ ሰው ተኝቶ እንኳን በሌላ ከተማ ቀን ከሆነ  ምርቱን ወይም አገልግሎቱን ያለማቋረጥ ሊሸጥ ያስችለዋል  
ሀገራችን ም ከዚህ እጅግ ዘመናዊ ከሆነበ ቴክኖሎጂ የንግድ ስርአት ተጠቃሚ ብትሆን በአገራዊ ምርቷ ላይ ጭማሬን ሊያስገኝና ለምርቷም ሰፊ ወደ ሆነው የአለም ገበያ ሊያስገባት ይችላል ። በጅማሬው ላይ ከሀገር ውስጥ ወደ ውጪ መግዛትን በማገድ ነገር ግን ከውጪ ሆኖ አንድ ሰው ወደ ሀገር ቤት የሚፈልገውን እንዲገዛ በማድረግ የውጭ ምንዛሬ ግኝታችንን ለማሳደግ ያስችላል ።  
 በድረ - ገፅ ግብይት አማካይነት መፅሀፍትን ብቻ ሳይሆን ማንኛውንም በቀላሉ በፖስታ ሊላኩ የሚችሉ እንደ ጫማ ፣ ከልሲና ፣ ሸሚዝ የመሳሰሉትንም ጭምር አንድ ሰው ከቤቱ ተቀምጦ ዋጋ በማነፃፀር መግዛት የሚቻልበት ደረጃ ላይ ተደርሷል - ባደጉት አገራት ። ይህንን ቴክኖሎጂ አዲስ አሰራርን በማስተዋወቅ የአለም የንግድ በድርጅት አባል በመሆን የሚገኘውን ጥቅም ማሳደግ ይቻላል ።
ከዚህ ጋር ተያይዞ የሚነሳው ጉዳይ ሀገራችን የባህር በር የሌላት አገር እንደመሆኗ ይህን ለማካካስ እንዲረዳት እጅግ ዘመናዊ የሆኑ የመገናኛ ፣ የኢንተርኔት ፣ የስልክ መሰረተ - ልማት ሊኖራት ይገባል ። ለዚህም ምክንያቱ የባህር የሌለው አገር ከውጪ ጋር ለመገናኘት እንደሌላው አገር ወደብ እንዳለው አገር በወደቡ ሊተማመን ስለማይችል ያለው አማራጭ እነኚህን የመገናኛ መንገዶች በመጠቀም ነው ንግዱንም ሆነ ከሌላው ሌላው ዓለም ጋር ያለውን ግንኙነት ማቀላጠፍ የሚችለው ።   
ከአውሮፓ እንደ ስዊዘርላንድ ምንም እንኳን የራሷ ወደብ ባይኖራትም ከኢትዮጲያ እጅግ ያነሰ የቆዳ ስፋትና የተፈጥሮ ሀብት ያላትና ተራራማ አገር ሆና ነገር ግን ከአውሮፓ ቀዳሚ የኑሮ ደረጃ ካላቸው አገራት አንዷ ለመሆን የበቃችው ያለባትን የተፈጥሮ ገደብን ማለትም በየብስ የተከበበችና ተራራማ ወደብ አልባ ብትሆንም እጅግ ዘመናዊ የመሰረተ ልማቶችን በመዘርጋት እንዲሁም ፣ በእውቀት ላይ የተመሰረቱ የኢንዱስትሪዎችን ማለትም በአለም የታወቀ የሰአትና የመድሀኒት የመሳሰሉት ኢንዱስትሪዎች ባለቤት ስትሆን በአገልግሎት ዘርፉም ከአለም እጅግ ስመ-ጥር የሆነና ተአማኒ የባንክና የኢንሹራንስ ኩባንያዎች ባለቤት ፣ እንዲሁም ምንም እንኳን የተባበሩት መንግስታት ድርጅት እና የአውሮፓ ህብረት አባል አገር ባትሆንም ፣  ከአውሮፓ አገራት ካሉ ዋነኛ አለም አቀፍ የዲፕሎማሲ መናኀሪያም ጭምር ለመሆን የበቃች ነች - ይህ ከኢትዮጲያ ጋር ተመሳሳይ ያደርጋታል ።
ለዚህ ሁሉ የስዊዘርላንድ ስኬት በአውሮፓ መሀል መገኘቷ ብቻ ሳይሆን ነገር ግን በእውቀት ላይ የተመሰረተ ፣ ዘመናዊ ኢኮኖሚን በመገንባቷ እና የተፈጥሮ ጉድለቷን ማካካስ በመቻሏ ወደብ አልባ አገራት እንኳን ሊደርሱ ከሚችሉት በላይ የላቀ የኑሮ ደረጃ ባለቤት ለመሆን የበቃች ነች ።