Monday, December 17, 2018

የለውጥ ሃይል

"የትም ፍጪው ዱቄቱን አምጪው "፦

ከወደቁ ወዲይ መላላጥ "ያማማቶ ነው መሪ የመረጠልን " ። ከወደቁ ወዲህ መንፈራገጥ ለመላላጥ አለ። ይህም መሪዎቹ (out of touch) ከእውነታው ጋር እንደተፋቱ እንደነበሩና አመላካች ነው ። ሌላው ባለስልጣን ደግሞ "አሜሪካ ከጅቡቲ ጦሬን አንቀሳቅሳለሁ ስላለች ነው አብይን የመረጥነው "ያሉ ባለስልጣንም አሉ ያም ሆነ ይህ ግን " የትም ፍጪው ዱቄቱን አምጪው " አለ ያገሬ ሰው።
እውነትም እንዳሉት ዶናልድ ያማማቶ ከሆነ መሪ የመረጠላቸው ነገሮች ከእጃቸው ወጥተው ነበረ ማለት ነው። ያማማቶ በ97ቱ ምርጫ በአዲሳባ የአሜሪካ አምባሳደር የነበሩ ሲሆን ትራምፕ ሲመጡ ግን ረዳት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሆነው ትልቅ ሹመትን ይዘው 97ቱ ምርጫ ከተቃዋሚዎች ጋር አልሰራም ብሎ የነበረውን ጊዜ ጠብቀው ሰርተውለታል ማለት ነው። " አለ ያገሬ ሰው ፥ አሁን ያማማቶ አካባቢውን  በሶማልያ የUSA አምባሳደር ሆነው ተሹመዋል።  በነገር ሽንቆጥ አድርገዋል። ምን ሲሉ " አንተም እንዳይመረጥ ተቃውመህ ነበረ " ሲሉ ደግፌ ነበረ ያሉትን  አጋልጠዋል ባደባባይ።  ብራስልስ  የአምባሳዳርነት ሹመት ሰጥቶኝ እምቢ ብዬ ነው ፥ የለውጡ ደጋፊ ነኝ ሲሉ ነበረ። ለበርካታ የለውጡ እንቅስቃሴ ክሬዲቱን ሃሳብ አመንጪነቱን ለብቻው ወስዶአል ፤ እስረኞች ይፈቱ ያልኩት እኔ ነኝ ወዘተ... ፥ለችግሮቹም ሌሎቹን እህት ድርጅቶቹን ተጠያቂ አድርጎአል ። ይሁን እንጂ ከህወሀት ሰፈር በተደጋጋሚ የሚሰማው ከፌደራል መንግስቱ የወጣ በተደጋጋሚ እየታየ ያለ አቁዋም ሃገር ላይ ችግርን እንዳያመጣና ትዝብት ላይ እንዳይጥል ሃገሪቱዋን።

No comments:

Post a Comment