Tuesday, March 12, 2013

የመሪነት ድክመቶች



አንድ መሪ ተከታዮቹን መውደድ ሲኖርበት የመሪነት እና የመምራት እድሉን ስለሰጡትም ለተከታዮቹ አክብሮት ሊኖረው ሲገባ ። የዚህ ስሜት የሌለው ከሆነ ግን እነሱን እሱን መተካት ሲችሉ ተከታዮቹ ግን እሱን በሌላ መሪ ሊተኩት ይችላሉ - የሱ ቦታ በቀላሉ በሌላ ሰው ሊተካ ይችላል፤ በተለይም የሀገር መሪ ከሆነ  ። ስለዚህ ራሱን ከተከታዮቹ አስበልጦ መውደድ የለበትም ። ታላላቅ የነበሩ መሪዎች እንኳን ሁሉ በታሪክ ውስጥ ከነሱ በተሻሉ ፣ ባነሱ ወይም ባልተሻሉ መሪዎች ተተክተዋል ። ስለዚህ ለራሱ እጅግ የበዛ ወይም የተጋነነ ቦታን መስጠት የለበትም ። ችግሮችን ከሚገባው በላይ አሳንሶ ማየት ወይንም ቸል ማለት አንድ መሪ ሊፈፅማቸው ከሚችላቸው ስህተቶች አንዱ ነው ።


የአይበገሬነት እና አይሳሳቴነት (Invincibility &Infallibility) ስሜት

በሰው ልጅ ታሪክ እንደታየው በአለም ህዝቦችም ሆነ ኩባንያዎች አመራር ታሪክ ውስጥ በጣም አንፀባራቂ ፣ ዳግመኛ አይፈጠሩም የሚባሉ ሰዎች ተከስተዋል ። ነገር ግን ሁሉም እንደ ሰው የእድሜ ዘመናቸውን ጨርሰው አልፈዋል ። መፅሀፍ ቅዱስ ላይ የጠቢቡ ንጉስ ሰለሞንን ያህል ግርማ ሞገስና ፣ ክ ብር እና እውቀት የነበረው ንጉስ በታሪክ እንዳልተከሰተ ይነግረናል ። ነገር ግን ጠቢቡ ሰለሞን ምንም እንኳን እጅግ ብልህ እና አዋቂ ቢሆንም መጨረሻ ላይ በሰራቸው ስህተቶች ክብሩ ዝቅ እንዳለና በመጨረሻም እንደማንኛውም መሪ እንዳለፈ በታሪክ የሚታወቅ ነገር ነው ። ከዘመናዊውም አለም የሚጠቀሱ በርካታ መሪዎች ተፈጥረዋል ። ስለዚህ መሪዎች የፈለገ ሀያል ፣ ገናና አዋቂ ቢሆኑም ያለው ትውልድ ስርአትንና ህግን ጠብቆ መኖር ስለሚፈልግ እነሱ ካለፉ ፣ በሌላ ተተክተው ኑሮ መቀጠሉ አይቀሬ ነው ።


አንድ መሪ ራሴን አይተኬ አድርጎ ከወሰደ (Indispensable) ነኝ ብሎ ካሰበ ፣ የማደርገው ነገር ሁሉ ትክክል ነው ወደሚል አስተሳሰብ ያመራል ። ይህም የሚያደርጋቸው ነገሮች ውጤታቸውን በአግባብና በቅጡ ሳያመዛዝን እንዲወስንና እንዲፈፅም ሲያደርገው ውሎ አድደሮም ከሚመራው ተቋም ወይም ሀገር ጥቅም አንፃር እሚፃረሩ ውሳኔዎችን እንዲወስንና ፣ ብሎም ከራሱ ጥቅም አንፃር ብቻ እንዲንቀሳቀስ ሊያደርገው ይችላል ። ይህ መሪዎች ሊፈፅሙት ከሚችሏቸው ስህተቶች ትልቁን ቦታ ይይዛል ። ለምሳሌ አንዳንድ አምባገነናዊ አገዛዝ በሚገዙ ሀገራት ውስጥ መሪዎች ለራሳቸው ትልቅ ስፍራን በመስጠት ከሀገርና ከሚመሯቸው ተቋማት በላይ በማሰብ ብዙ ስህተትን እንዱሰሩና ተቃውሞ እያቆጠቆጠባቸው እንዲሄድ ያደርጋል ። 



እነኚህ ስሜቶች አንድ መሪን አደጋ ውስጥ ሊከቱ የሚችሉ ናቸው ፣አንድ ማንኛውም ሰው እንደ ሰው የሚቆጠር ነው ። የሰው ባህርያቶችንም የያዘ ነው ። እንደሰው ይታመማል ፣ ያረጃል ፣ ይሳሳታል ወዘተ … ሰውለሆነም አንድ ሰው ራሱን ከሌሎች የተለየና ሌሎችን የሚጣያጋጥሙ ችግሮች እርሱን እንደማይመለከቱት አድርጎ ማሰብ የለበትም ። አንድ መሪ ተከታዮቹ በሱ አመራር እምንትን በሚያጡበት ጊዜ ውሳኔዎቹ እማይተገበሩ ሲሆን ፣ ትእዛዞቹም ተፈፃሚነታቸው እየቀረ ይሄዳል ። ይህን ሁሉ መሪው ራሱ ወዲያውኑ ላያውቀው ይችላል ። ውሎ አድሮ ሊረዳው ይችላል ። እዚህ ደረጃ ከደረሰ የመሪነቱን ወይም የአመራሩን ውድቀትደረጃ እሚያሳይ ነው ።
ዳዊት በመዝሙሩ «ንጉስን የሰራዊት ብዛት  አያድነውም » ይላል ። ይህም አግባብ የሆነውን ነገር ከማድረግ ይልቅ ባለው ነገር መመካትና ምንም አልሆንም ብሎ ማሰብ የለበትም ።


ግትርነት ወይም ችኮነት (Stubbornness)

ሌላው ደግሞ ለአንድ መሪ ወቅቱን ከመረዳት ጎን ለጎን ራሱን ከሁኔታዎች ጋር ማስማማትና ማዛመድ ያስፈልገዋል ፤ ራሱን ማስማማት ፣ ማዛመድ (Flexibie) መሆን አለበት ፣ ነገር ግን ከእውነታው ውጪ ግትር ከሆነ ግን ራሱን ማዛመድና ማስማማት (Adapt) የማድረግ ብቃቱን ይቀንስበታል በተከታዮቹም ሀፖነ በሌሎች ተመልካቾች ዘንድ እንደ የለውጥ እንቅፋት ተደርጎም ሊቆጠር ይችላል ። ግትርነት ለህመም እንደሚዳርግም በሀኪሞች የታወቀ ነገር ነው ።


ከልክ ያለፈ ጥርጣሬ (Paranoia)

ጤነኛ የሆነ ጥርጣሬ አንድን መሪ ሊመጡ ከሚችሉ አደጋዎች ይጠብቀዋል ። ነገር ግን ጥርጣሬ በመሪው ቁጥጥር ስር ያለ ነገር መሆን አለበት ። ከልክ ያለፈ ጥርጣሬ አንድ መሪን ትክክል በሆነውና ባልሆነው፣ መጥፎ በሆነውና ባልሆነው፣መሆን ባለበትና መሆን በሌለበት ፣በወዳጆችና በተቀናቃቀኞች መሀከል ያለውን ልዩነት እንዳይረዳ ያደርገዋል ። ሁሉንም ነገር በመጥፎ ብቻ እንዲያይና አላስፈላጊ እርምጃዎችን እንዲወስድ ያደርገዋል ። በአጭሩ ካለው እውነታ ውጪ የሆነ አስተሳስብን እንዲይዝ ያደርገዋል ።


ለዚህ ብዙ ጊዜ በምሳሌነት የሚጠቀሰው የቀድሞዋ ሶቭየት ህብረት መሪ ለዚህ ብዙ ጊዜ በምሳሌነት የሚጠቀሰው የቀድሞዋ ሶቭየት ህብረት መሪ የነበረው ጆሴፍ ስታሊን ነው ። በጥርጣሬ ብቻ በርካቶችን ለሞት የዳረገው ስታሊን አሁን አሁን እየወጡ ያሉ የህክምና መረጃዎች የሚያሳዩት የአእምሮውን ጤነኛነት የጥያቄ ውስጥ የሚያስገቡ የህክምና መረጃዎች እየወጡ ነው ። ሀኪሞቹ እንደሚሉት የዛን ጊዜዋ ሀያል ሀገርጤንነቱ አጠያያቂ በነበረ ሰው እጅ እንደነበረች ነው ። ብዙውን ጊዜ አምባገነናዊ የሆኑ መሪዎች በዚህ አጉል ጥርጣሬ ተጠቂዎች ናቸው ።

No comments:

Post a Comment