Thursday, February 28, 2013

የታሪክ ጠባሳ የሚፈጥረው አሉታዊ ጥላ




            ብዙ ጊዜ ተገዢ ወይንም ተጨቋኝ ውሎ አድሮ የሞራል የበላይነትን ያጎናፅፋል ። ገዢው ስልጣኑን ወይንም ሀብቱን ለመከላከል ሲል በሚያደርጋቸው ድርጊቶች ሳያስበው ስህተቶችን ይፈፅማል ። እነኚህም ስህተቶች ውለው አድረው ጉዳት የደረሰበት ወገን የሞራል የበላይነትን እንዲይዙ ያደርጉታል ። ሲጀመር ፍትህን ይዞ የተነሳው ገዢ ቀስ በቀስ  ራሱ ወደ ቀድሞው ፣ራሱ ወዳስወገደው አይነት ፈላጭ ቆራጭነት ይመለሳል ። በዚህ የሞራል የበላይነቱን ልእልናን ወደ ተገዢዎቹ ወይም ወደ ተጨቋኞቹ ይተላለፋል ።በእንደዚህ አይነት ሁኔታ ገዢና ተገዢ ቦታቸውን የሚቀያየሩ ሲሆን  ፣ ገዢ የሆኑት ዎች ይህንን ነባራዊ እውነታ ካልተረዱ ።  ለለውጡም ሁኑታ ቅድመ ሁኔታ እሚያስፈልጉት ህሊናና እየተዘጋጁ ይሄዳሉ ።
           ይህ ብቻ ሳይሆን አንድ ስርአት የሚፈጥረው ማህበረሰብ ራሱ ውሎ አድሮ ከስርአቱ ጋር ሆድና ጀርባ የመሆን እድልም አለ ። ለምሳሌ በብዙ ሀገራት ቀድሞ መካከለኛ መደብ ያልነበረባቸው ፣ እንዲሁም የዲሞክራሲ ስርአትም ያልነበራቸው ሀገራት ፣ በመሪዎቹ ፖሊሲ ምክንያት ሀገራቱ የምጣኔ - ሀብት ብልፅግናን ሲያመጡ መጀመሪያ ላይ ከመካከለኛው መደብ ጠንካራ ድጋፍን ሲያገኙ ውለው አድረው ግን ያ የተፈጠረው የመካከለኛው መደብ ጥያቄዎቹ እያደጉ መጥተው ካለው ስርአት ጋር  የሚቃረኑ እና ስርአቱ እንዲለወጥ ወይንም እንዲሻሻል ፍላጎት ይፈጠራል ። ይህም ለምሳሌ በሩስያ ከቀዝቃዛው ጦርነት ማብቃት በኋላ የፑቲን አስተዳደር ስርአትን በማስፈንና ፣ በእዳና በምጣኔ - ሀብት ዘቅጣ የነበረችውን ሀገር ወደ ቀድሞው ገናናነቷ መመለስ ቢችልም እንዲሁም መካከለኛው መደብ ቢደግፈውም ፣ ከተወሰኑ አመታት በኋላ ግን ስርአቱ ለመካከለኛው መደብ እንቅፋት ሊሆን እንደሚችልና ለእድገቱም እንቅፋት እንደሚሆን  የተረዳው ህብረተሰብ ድጋፉ እየቀዘቀዘ መምጣቱ አልቀረም ፤ በቻይናም የዚህ ምልክቶች በመታየት ላይ ናቸው ።

               በአሜሪካ አፍሪካ አሜሪካውያን አሁን ወደ ከፍተኛ ስልጣን ደረጃዎች እየመጡ ሲሆን ፣ከዚህ ቀደም እንኳን ለመመረጥ ቀርቶ መምረጥ እንኳን እማይችሉበት ጊዜ ነበረ ። በደቡብ አፍሪካም እንዲሁ ጥቁሮች እንደ ሁለተኛ ዜጋ ይቆጠሩ የነበረ ሲሆን የዘር መድልኦ በራሳቸው ሀገር ይደረግባቸው የነበረ ቢሆንም የኋላ ኋላ ግን የገዛ ሀገራቸው ባለቤትና አስተዳዳሪዎች ለመሆን በቅተዋል ። 

ይህ ክስተት በተደጋጋሚ በታሪክ የታየ ሲሆን ምእራባውያን ካለፉት ልምዶቻቸው ይህንን ስለሚያውቁ በርካታ ጥንቃቄዎችን እሚያደርጉት ። በባሪያ ንግድ ፣ በቅኝ ግዛት  እና በከዚያም በኋላ በዘረኝነትና በመሳሰለው በርካታ ጉዳትን ስላደረሱ በዛም ለበርካታ የሞራል የበላይነታቸውን ስላጡ ያንን ላለመድገም በእጅጉ የሚጠነቀቁት ። ጆርጅ ኦርዌል የተባለው ታዋቂው እንግሊዛዊ ደራሲ ያለፈውን የሚቆጣጠር የአሁኑን ይቆጣጠራል፣ የአሁኑን የሚቆጣጠር የወደፊቱንም ይቆጣጠራል ይላል ። ያለፈውን የተቆጣጠረ የአሁንን ብሎም የወደፊቱን መቆጣጠር ይችላል ።

ለምሳሌ በአሁኑ ወቅት ከዚህ በፊት እንደ አናሳ ዜጋ ይታዩ የነበሩት ጥቁሮች በአሜሪካን ሀገር ከፍተኛውን የስልጣን ደረጃ ውስጥ እየገቡ ሲገኙ ፣ ይሄም ለዘመናት ተገዢ የሆኑት ጥቁሮች ገዢም ፣አስተዳዳሪም ሊሆኑ እንደሚችሉ የሚያሳይ ነው ። በምእራቡ አለም በርካታ መፅሀፍት በየአመቱ ይታተማሉ ። ቁጥራቸው ቀላል እማይባሉት ግለ - ታሪኮች የመሳሰሉት ናቸው ። ነገር ግን አንድ ሰው መፅሀፍ ሲፅፍ ካለፈው በመነሳት ፣ታሪክን በራሱ መንገድ በመተርጎም የወደፊቱን ሰው በተረዳው መንገድ ለመቅረፅ ካለው ጉጉት በመነሳት የሚያደርገው ጥረት ነው ።
ያለፈውን እሚቆጣጠር ፣ ባለፈው እንደዚህ ስለተደረኩ ነው አሁን እንደዚህ እማደርገው ወይም አሁን እንደዚህ መሆን ያለበት እሚል ክርክር ሲያቀርብ ፣ አሁን እሚደረግ ማንኛውም ነገር ደግሞ ለወደፊት ለሚሆነው በጎም ሆነ ጥሩ ነገር መሰረትን ይጥላል ። ለዚህም ነው ታሪክ ላይ ብዙ መራኮትና ታሪክን ሁሉም በየራሱ መንገድ ለመተርጎም የሚጥረው ።

ነገር ግን እዚህ ላይ መታወቅ ያለበት ነገር ባለፈው የተደረገ ወይም የተከሰተ መጥፎ ነገር አሁን ለሚደረግን ትክክል ወይም አግባብ ያልሆነ ነገር እንዲደረግ ፣ ትክክለኛ (Justify) አያደርገውም ።በተለምዶ ሁለት ስህተቶች አንድን ነገር ትክክል አያደርጉትም እንደሚባለው መሆኑ ነው ። ለምሳሌ እስራኤላውያን በአውሮፓውያን ለብዙ ክፍለ ዘመናት መሰቃየታቸው ብሎም አለምን ለመቆጣጠር እያሴሩ ነው በሚል በሁለተኛው የአለም ጦርነት በጀርመን ናዚዎች መፈጀታቸው ፣ እነሱ ፍልስጥኤም ላይ የሚያደርጉትን ማንኛውንም ነገርወይም እሚያደርሱትን ችግር ትክክለኛ ወይም ፍትሀዊ አያደርገውም ። ወይም አውሮፓውያን እስራኤልን በፍልስጥኤም ላይ እምታደርገውን ነገር በጭፍን ቢደግፉ እነሱ ለብዙ ክፍለ ዘመናት በአይሁዶች ላይ ያደረሱትን ስቃይና ግፍ አያጥበውም ። አንዳንዶች እንደውም እስራኤል በዚህ ድርጊቷ የኋላ ኋላ መልካም ውጤትን እንደማያመጣላት እየገለፁ ይገኛሉ ። 

ጀርመኖችንም ብንወስድ ምንም እንኳን እሁዳውያንን መጥላት ለብዙ መቶ አመታት በአውሮፓ የነበረና የተለመደ ቢሆንም አሁንም ድረስ ያለ ቢሆንም ናዚዎች ግን ይሄንን ነገር ወደ ከፍተኛ ጥግ በመግፋት እሁዳውያንን በሁለተኛው የአለም ጦርነት ወቅት እሁንዳውያንን በመጨፍጨፋቸው ፣ እስካሁን ድረስ እያፍሩበት ያሉበት ጉዳይ ነው፣ ጀርመን በዚህ ምክንያት በርካታ ዋጋን ከፍላለች ። በርካታ ገንዘብም ለጦር ጉዳት የከፈሉ ሲሆን ይሄንን ድርጊትን የካደ ራሱ በህግ እንዲጠየቅም ጭምር ጀርመን ደንግጋለች ፣ ይሄንን ድርጊትን የካደ ራሱ በህግ እንዲጠየቅም ጭምር ደንግጋለች ፣ ይሄ ብቻ ሳይሆን ጀርመን ከሁለተኛው የአለም ጦርነት የደረሳባትንና ያለፈችበትን ያንን በመፍራት እንደ ሌሎች የአውሮፓ ሀገራት በአለም ጉዳዮች ላይ ጠንካራ ተሳትፎ የላትም ፤ ለምሳሌ እንግሊዝና ፈረንሳይን ብንወስድ ምንም እንኳን ከጀርመን ከእነሱ የበለጠ የምጣኔ - ሀብት አቅም ቢኖራትም የእነሱን ያክልግን ተሳትፎን አታደርግም ።

ምንም እንኳን ቱርክ ብታስጠነቅቅም ፣ ፈረንሳዮችም በ20ኛው ክፍለ ዘመን መጀመሪያ ላይ አርሜንያውያን በቱርኮች የተጨፈጨፉበትን ድርጊት የካደ ማንኛውም ሰው በህግ እንዲጠየቅ እነሱም ደንግገዋል ። በነገራችን ላይ ይህ የአብዝሀው አናሳዎቹን መጨቆን ፣ ውሎ አድሮ በተራው የአናሳዎቹን አገዛዝ ፍትሀዊ ወይንም ተቀባይነት ያለው እንዲሆን ያደርገዋል ። ነገር ግን የዚህ አይነቱ አገዛዝ ችግሩ ግን የአናሳዎቹ አገዛዝ ራሱን ከብዙሀኑ ጋር ማዋሀድ «አሲሚሌት» ማድረግ ይኖርበታል ፣ አለበለዚያ በረጅም ጊዜ ህልውናውን አስጠብቆ መቆየት አይችልም ። ቢያንስ ፍትሀዊነትን መላበስ ይኖርበታል ። ለምሳሌእስራኤልን ብንወስድ ምንም እንኳን የአረብ ህዝብ ቁጥሩ ስለሚያይል በአረብ ህዝብ መዋጥ ባትፈልግምና እስራኤልን የአይሁዶች ብቻ አገር የማድረግ ፍላጎት ያላት ብትሆንም ፣ በረጅም ጊዜ ግን በአካባቢው በሰላም ለመኖር ያስችላት ዘንድ ፣ ከጎረቤቶቿ ፍልስጥኤሞችን ሆነ አረቦች ጋር ያላት ግንኙነት የተሻለ ፍትሀዊነት የሰፈነት መሆኑ ግድ ነው ። 

            እስራኤል በበኩሏ  ይህንን ችግር ለመጋፈጥ ወታደራዊ ጡንቻዋን ማፈርጠሙን እንደ ዋና አማራጭ ወስዳዋለች ማለት ይቻላል ።የመከላከያ ባጀቷን ከቱርክ በ73 እጥፍ  ከእንግሊዝ በ 11 ጊዜ እጥፍ ታንሳለች አመታዊ 16ቢሊየን የአሜሪካን ዶላር ወይም 288 ቢሊዮን የኢትዮጲያ ብር በጀት ትመድባለች ። ነገር ግን እስራኤል ከግብፅ ጋር በምትዋሰንበት ድንበር ላይ የደህንነት ጥበቃ ሰውራ ስራዋን ለመስራት ፣ እንዲሁም የአረብ አመፅ አካባቢው መናዊ ወጡ የእስራኤልን ስጋት አንሮታል ። የካይሮን ቃል በመተማመኛነት ተቀብላ ከመቀመጥ ይልቅ ፣ የራሷን የመከላከያ ባጀቷን ማሳደግንና ራሷን መከላከልን መርጣለች ። በወታደራዊ በአለም 10ኛ ስትሆን 10 የኒውክሎሊየር አረሮች ባለቤትም ነች ። ከዚህም በተጨማሪ  በመቶዎች የሚቆጠሩ የጦርነቶች ፣ የጦር መርከቦች ያሏትም ሀገር ነች ።


No comments:

Post a Comment