Thursday, September 12, 2019

The Ethiopic Calendar

The Ethiopic Calendar

By Dr. Aberra Molla

Ethiopia has its own ancient calendar. According to the beliefs of the Ethiopian Orthodox Church, God created the world 5500 years before the birth of Christ and it is 1994 years since Jesus was born. Based on this timeline, we are in the year 7494 of the eighth millennium (or ስምንተኛው ሺህ). These are referred to as Amete Alem (ዓመተ ዓለም) in Amharic or "the years of the world". Era of the world dates from 5493 B.C.

Ethiopic is not the only calendar in Ethiopia either. The works of Enoch(ሄኖክ) had been in Ethiopia and Egypt before the times of Moses and on through the times of King Solomon and Queen of Sheba. As has been the case for Israel, Egypt and Ethiopia have had important roles in Biblical History. An Enochian year is completed in 364 days, Enoch 82:4-7 andJubilees 6:23-28. More precisely, a 365-day-solar-year and the 365-year-solar-cycle appear as a 365-days-and-years single term. From the three books of Enoch, a curious 364-day length of calendar year lends new insight by reserving the last day of the solar year. Ethiopians followed the Old Testament before the introduction of Christianity (1 Kings 10:1-9). The Arc of the Covenant was brought to Ethiopia long before Christianity accepted the Old Testament and offered worship to God. The Oromo (ኦሮሞ) people have their own calendar. Bete Israel (ቤተ እሥራዔል) believe in the Jewish faith. 

Tuesday, August 20, 2019

የዓለም የሕዝብ ቁጥር

መቀመጫውን በዋሽንግተን ዲሲ ያደረገው ፒው የጥናት ማዕከል ይፋ ያደረገው መረጃ እንደሚጠቁመው የኢትዮጵያ ሕዝብ ቁጥር በጎርጎሮሳዊው 2100 ዓ.ም. 294 ሚሊዮን ይደርሳል ,

በተጠቀሰው ጊዜ 527 ሚሊዮን ዜጎች የሚኖሯት ናይጄሪያ በሕዝብ ብዛት ከአፍሪካ ቀዳሚ ትሆናለች። ከአፍሪካ ዴሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎ፣ ታንዛኒያ፣ አንጎላ፣ ኒጀር፣ ግብፅ እና ሱዳን የሕዝብ ቁጥራቸው በከፍተኛ ፍጥነት ከሚያድግባቸው ሃገራት መካከል ቀዳሚ ናቸው።

በመረጃው መሠረት የምሥራቅ አውሮጳ ሃገራት የሕዝብ ቁጥር በከፍተኛ ደረጃ ይቀንሳል። አልባኒያ፣ ሰርቢያ፣ ሞልዶቫ እና ቦስኒያ ሔርዝጎቪና በ2100 ዓ.ም. የሕዝብ ቁጥራቸው በከፍተኛ ደረጃ ከሚቀንስባቸው መካከል ይገኙበታል።

የዓለም ስነ-ሕዝብ ቀን በዛሬው ዕለት ሲከበር የተባበሩት መንግሥታትን ጨምሮ ዓለም አቀፍ ተቋማት የሕዝብ ብዛት መጨመር በሰው ልጅ አኗኗር እና በልማት እቅዶች ላይ ስለሚኖረው ጫና ግንዛቤ ለማስጨበጥ ይሠራሉ።

የተፈጥሮ ሐብት መመናመን፣ የሐብት ክፍፍል መዛባት፣ መሠረታዊ ግልጋሎቶች አለመሟላትን የመሳሰሉ ቀውሶች በሕዝብ ቁጥር መብዛት የበለጠ እንደሚጠናከሩ የተባበሩት መንግሥታት መረጃ ይጠቁማል።

How Africa Shaped the Christian Mind Rediscovering the Africa Seedbed of Western Christianity Thomas C

J. Scott HorrellJ. Scott Horrell . Oden Downers Grove, IL 2008-01-11 Oden brings his patristic expertise and focused studies in African Christianity to bear in this pioneering book. Oden is the retired Henry Anson Buttz professor of theology at the Theological School of Drew University and author of numerous works including The Rebirth of Orthodoxy (San Francisco: HarperSanFrancisco, 2003) and a three-volume Systematic Theology (Peabody, MA: Hendrickson, 2006). He is also the general editor of the twenty-nine-volume Ancient Christian Commentary on Scripture (Downers Grove, IL: InterVarsity Press, 1998- ), and the forthcoming Ancient Christian Doctrine series on the Nicene Creed. He was Dallas Seminary’s 2009 Griffith Thomas lecturer. How Africa Shaped the Christian Mind argues that the formative flow of early Christian thought was from south to north, rather than the commonly assumed belief that Christianity is a European transplant on African shores. Oden sets forth seven ways that African Christianity informed Western and world Christianity: (1) the Western concept of the university; (2) Christian exegesis of Scripture; (3) early Christian doctrine (Tertullian, Origen, Cyprian, Athanasius, Augustine); (4) modeling conciliar patterns for ecumenical decision-making; (5) birth and development of monasticism; (6) Christian Neoplatonism; and (7) the development of rhetorical and dialectical finesse. The book asserts the indigenous nature of African Christianity that developed along the Nile and Medjerda valleys and extended through Ethiopia and Sudan, possibly moving southward into sub-Sahara Africa through Bantu migration. Repeatedly the author affirms that “African Christianity has arisen out of distinctly African experience on African soil” (p. 13), that is, North Africa is as fully African as is southern Africa (p. 79). Indeed, the very term “Africa” was first applied to the Tunisian peninsula and gradually evolved to include the entire continent. Oden invites a new wave of scholarship regarding African Christianity in that much is literally buried under the sand or may exist deep within sub-Sahara African traditions. It is easily forgotten that Alexandria was once the intellectual center of the world and a major location for both Jewish and Christian populations. The work opines that now is the time for the recovery of African orthodoxy, especially given the rapid expansion of African Christianity, the new hunger for intellectual depth, and “the perceived might of the Muslim world, coupled with the exhaustion of modern Western intellectual alternatives” (p. 101). Besides hoping for a renewed African orthodoxy rooted in its early fathers, Oden suggests that Christianity be reconciled with Islam, at least in the sense of “setting more realistic parameters of the tests that Christians face with Islam” (p. 134). Speaking of government intimidation of Christians in North Africa, Oden writes that Christians must “be protected by law, by police security and if necessary by proportional means of guaranteeing freedom of religion” (p. 136). With these various factors the author sets forth a tentative agenda for a consortium of scholars (especially African scholars) to plumb afresh the riches of the African heritage. The book includes an appendix that traces African Christian development from Mark (the apostle to Egypt) and Apollos (Acts 18) onward to Philotheos, patriarch of Alexandria in A.D. 1000. An excellent bibliography and six maps are helpful in visualizing the locations of Nilotic and Numidian Christian centers. How Africa Shaped the Christian Mind is a helpful challenge to consider the primacy of African theology in the first centuries of the church. Repeatedly Oden chides academics for its Eurocentric assumptions. “Even black nationalist advocates who have exalted every other conceivable aspect of the African tradition seem to have consistently ignored this patristic gift lying at their feet” (p. 11). Such repetition at times is belabored and, the point being made, detracts from the fertile content of the work. Yet the author’s intent is to encourage the nearly half billion African believers. Oden also recognizes the current lack of evidence to affirm Africa as a primary seedbed of Christianity. Given the centuries of interplay between Alexandria, Athens, Palestine, Carthage, and Rome, acute readers will wonder if the case that North African theology was distinctly African may be overstated. Yet this book is a very good beginning to what Oden sees as a multigenerational task. Christian workers focused on Africa and the Middle East will find it most helpful. Book reviews are published online and in print every quarter in Bibliotheca Sacra. Subcribe Today J. Scott Horrell J. Scott Horrell Professor of Theological Studies, Dr. Scott Horrell was born in Wenatchee on the Columbia River and grew up in Ephrata and Quincy in central Washington State. He is a graduate of Seattle Pacific University. He has pastored five times, twice in urban Brazil. Now he has enjoyed 22 years at DTS with about the same number of years in ministry outside the US, centered on teaching Bible doctrine, theology, church planting, and pastoral training. He is currently an adjunct professor of doctoral studies at SETECA in Guatemala, and occasional adjunct professor at others schools in various parts of the world. He and his wife Ruth are grateful for their two daughters, two son-in-laws, and eight grandchildren. Review Jul 21, 2018 D. Scott BarfootD. Scott Barfoot Teams That Thrive: Five Disciplines of Collaborative Church Leadership. One of the greatest theological insights embodied in the triune God, the biblical institution of marriage, and the local church is the worship-inspiring and transformational... Review Jul 21, 2018 Joseph D. FantinJoseph D. Fantin Acts: An Exegetical Commentary. Volume 4: 24:1–28:31. Now complete, Craig Keener’s four volume, 4501 page (xlii + 4459), 10¾ inch (27.5 cm) wide, 19 lb (8.62 kg) commentary, with more than 45,000 ancient nonbiblical references on... Arts & Media Jul 9, 2019 Patrick ThomasPatrick ThomasRyan FlaniganDarrell L. BockMikel Del Rosario Generational Unity in Worship Music - Classic Spiritual Life Jul 3, 2019 Daniel L. HillDaniel L. Hill The Names We Call Ourselves Dr. Daniel Hill, assistant professor of Theological Studies, highlights of the primary tasks of the people of God, which is to remember how identity is defined by relationship to... Theology Jul 2, 2019 Daniel DarlingDaniel DarlingDarrell L. Bock Human Dignity and Cultural Engagement Spiritual Life Jun 28, 2019 Mark L. BaileyMark L. Bailey Alive to Forward To put it in a simple metaphor, before we came to Christ, the Bible teaches that all of our life was a life of driving in reverse. The doctrine of depravity doesn’t teach that... DTS Voice offers biblically-centered articles, stories, podcasts, and points of view from the DTS family designed to encourage and equip the church for gospel transformation. Sign up for DTS voice updates Copyright Dallas Theological Seminary -- Sent from Fast notepad

Friday, July 12, 2019

ወደ ኋላ የመመለስ ስጋት

ኢትዮጵያ ጋዜጠኞችን በማሰር፤ የጸረ-ሽብር ሕጓን መልሳ ሥራ ላይ በማዋል እና የኢንተርኔት ግልጋሎትን በማቋረጥ ወደ ቀደመው የመገናኛ ብዙኃን ነፃነት አፈና የመመለስ አደጋ እንደተጋረጠባት የጋዜጠኞች መብት ተቆርቋሪ ድርጅት ፣ (CpJ ) አስጠነቀቀ።

በአሁኑ ወቅት በትንሹ ሦስት ጋዜጠኞች በእስር ላይ እንደሚገኙ የጋዜጠኞች መብት ተሟጋቹ ሲፒጄ (CPJ) አስታውቋል። ሌሎች ሦስት ጋዜጠኞች ታስረው ቢፈቱም አሁንም የፍርድ ቤት ሙግት እንደሚጠብቃቸው ከሰሐራ በታች የሚገኙ የአፍሪካ ሃገራት የድርጅቱ ተወካይ ሞቶኪ ሙሞ ለዶይቼ ቬለ ተናግረዋል።

ሞቶኪ ሙሞ እንደሚሉት ኢትዮጵያውያን ጋዜጠኞች ሥራቸውን በአግባቡ ለመከወን ፈተና በዝቶባቸዋል።
ሞቶኪ ሙሞ «ባለፈው ሰኔ የኢንተርኔት አገልግሎት መቋረጡ የመገናኛ ብዙኃን ነፃነትን እጅግ ጎድቷል።

ጋዜጠኞች ሥራቸውን ለመሥራት፣ ከመረጃ ምንጮቻቸው ለመገናኘት፣ መረጃዎቻቸውን ለማጣራት ሰበር ዜናዎችን በፍጥነት ለማተም ፈተና ሆኗል። በግንቦት እና በሰኔ ወራት የታሰሩ ጋዜጠኞች አሉ።

ቢያንስ አንድ ጋዜጠኛ እና ባልደረባው በሥራቸው ሳቢያ ክስ ተመስርቶባቸዋል። በቅርቡ ከዚህ ቀደም ለመገናኛ ብዙኃን ብዙ ችግር ሲፈጥር በቆየው የጸረ-ሽብር ሕግ ጋዜጠኞች መታሠራቸውንም ደርሰንበታል።» ብለዋል ።

የጋዜጠኞች መብት ተሟጋቹ ያነጋገራቸው ኢትዮጵያውያን ባለሙያዎች እና የሰብዓዊ መብት ተሟጋቾች ባለፈው አንድ ዓመት የመገናኛ ብዙኃን ነፃነት መሻሻል ቢያሳይም የመንግሥቱ የቀደሙ ልምዶች የማገርሸት ምልክት ማሳየታቸውን ተናግረዋል።

የጠቅላይ ምኒስትር ዐቢይ አሕመድ መንግሥት በጀመራቸው ማሻሻያዎች ለውጥ ይደረግበታል የተባለው የጸረ-ሽብር ሕግ መልሶ ጋዜጠኞችን ለማሰር ግልጋሎት ላይ መዋሉ አሳሳቢ መሆኑን ጠቁመዋል። ሞቶኪ ሙሞ «አዎንታዊ መሻሻል ወደታየበት፣ መንግሥት ጋዜጠኞችን ወደማያስርበት እና ኢትዮጵያ የመገናኝ ብዙኃን ነፃነት የተከበረባት አገር ትሆን ዘንድ ሊያረጋግጥ ወደሚችለው የማሻሻያ እርምጃ እንመለስ ማለት እንፈልጋለን።

በእርግጥ የመገናኛ ብዙኃን ነፃነት መፃኢ እጣ-ፈንታ አሳስቦናል፤ የዛኑ ያህል የታዩ ለውጦችንም እንረዳለን። የምናነሳቸው አሳሳቢ ጉዳዮች ምላሽ አግኝተው ኢትዮጵያ የመገናኛ ብዙኃን ነፃነት የተከበረባት አገር ትሆናለች ብለን ተስፋ እናደርጋለን።» ሲሉ በአጽንዖት ተናግረዋል።

የሰብዓዊ መብት ተሟጋቹ አምነስቲ Amnesty International  ኢንተርናሽናል የኢትዮጵያ መንግሥት እርምጃ አገሪቱ ባለፈው አንድ ዓመት ገደማ ያሳየችውን መሻሻል ሊቀለብስ እንደሚችል በትናንትናው ዕለት አስጠንቅቆ ነበር። ወደ ኅንላ እንዳንመለስ ጎበዝ።

Wednesday, July 10, 2019

ምን ሊሆን ይችላል

መፈንቅለ መንግስታት ያደረሱት የኢኮኖሚ ጉዳት
በቅርብ ግዜያት የተደረጉት መፈንቅለ መንግስታት ለኢንቨስትመንት ፀር ነው - በተለይም የውጭ ኢንቨስትመንት ፤ የቱሪዝም ፍሰቱን ይቀንሳል ። መፈንቅለ መንግስት ተደረገ የሚል ዜና መሰማት እንኳን የሀገርን ገፅታ በእጅጉ ይጎዳል ። ለዚሕም ምሳሌዎቹ በቱርክ ፤ በታይላንድ ፤ በግብፅ እና በሱዳን የትድረጉት ኣይነተኛ ምሳሌዎች ናቸው ።
ጃንሆይ እንኳን የተሞከረባቸውን የ53ቱን የነ መንግስቱ ንዋይን ሙከራ "የታህሣሡ ግልግር " ከማለት ውጭ  መፈንቅለ መንግስት ነው አላሉም።

Sunday, July 7, 2019

ራስ -ተፈርያውንና ጃንሆይ

‌«ወደ አህጉረ አፍሪካ ተመልከቱ አንድ ጥቁር ይነግሣል፤ ነፃነትም ይሆናል» ጃማይካዊው የመብት ታጋይ ማርከስ ጋርቬይ ነበር ይህን የተነበየው።  ኢትዮጵያን ከአራት አሥርት ዓመታት በላይ የገዙት ቀዳማዊ አፄ ኃይለ ሥላሴ በ1923 ዓ. ም. የንግሥና ዙፋናቸውን ጫኑ።

የእሳቸው ንግሥና ዜና አህጉረ አፍሪካን አልፎ ጃማይካ ደረሰ። ወሬውን የሰሙ የራስ ተፈሪ እምነት ተከታዮች ፈጣሪ በሥጋ ተገልጿ፤ ጠባቂያችን ነግሧል በማለት ወደ ኢትዮጵያ ጎረፉ። ራስ ተፈሪያን ጃህ እያሉ የሚጠሯቸው ጃንሆይ፣ በፈረንጆቹ 1966 ዓ. ም. ወደ ጃማይካ አቀኑ። ሥፍር ቁጥር የሌለው ሰው ተቀበላቸው። ባዩትም ነገር እጅግ ተደነቁ። እሳቸው ወደ ኪንግስተን ባቀኑ ጊዜ የሰማይ ውሃ ዓይንሽን ለአፈር ብሏት የነበረችው ጃማይካ በዝናብ እንደራሰችም ይነገራል።

የሬጌ ሙዚቃ ንጉሡ ቦብ ማርሌም በሙዚቃው አፍሪካን እና ኢትዮጵያን እንዲሁም ንጉሡን የመፃኢ ዘመን ተስፋ እና መጠጊያ አድርጎ ይስላቸው ነበር። ለአፍሪካ አንድነት በሠሩት ውለታ ሊታወሱ ይገባል ተብሎ በቅርቡ ሃውልት የቆመላቸው ጃንሆይም ወደ አፍሪካ መመለስ ለሚሻ ጥቁር ይሁን በማለት ሻሸመኔ አካባቢ 200 ሄክታር ገደማ መሬት ለገሱ።

የራስ ተፈሪ እምነት ተከታዮች ከደቡባዊ የአፍሪቃ ክፍል እስከ ምዕራቡ ጥግ፤ ከሰሜን እስከ ምስራቅ ይገኛሉ። እንደ ሻሸመኔ ግን ያለ አይመስልም።
መጀመሪያ ላይ 12 ጃማይካዊያን ብቻ ወደ ሻሸመኔ እንዳቀኑ ይነገራል። ኋላ ላይ ግን የትየለሌ ራስ ተፊሪያኖች ጉዟቸውን ወደ ሻሸመኔ አደረጉ።

አሁን ላይ ሻሸመኔ ውስጥ በርካታ የራስ ተፈሪ እምነት ተከታይ ጃማይካዊያን ይኖራሉ። አሁን ግን ትኩረቱ ከአራት አሥርት ዓመታት በላይ ከቆዩባት ሻሸመኔ ወደ ሐረር የዞረ ይመስላል። ለምን?

ከሻሼ ወደ ሐረር  ራስ እዝቄል ኩማ ለበርካታ ዓመታት ኢትዮጵያ ውስጥ የኖረ የራስ ተፈሪያን እምነት ተከታይ ነው። ኢትዯጵያ ውስጥ ወልዶ ከብዷል። ሕይወቱን መሥርቷል። ከሻሸመኔ ወደ ሐረር የሚደረገውን መንፈሳዊ ጉዞ የሚመራው ራስ እዝቄል ኩማ ለራስ ተፈሪያን ማሕበረሰብ ከሻሸመኔ ይልቅ ሐረር የተሻለ ቅርበት እንዳላት ይናገራል።

«ልንሆን የሚገባው ሐረር ነው። ጃህ፤ ንጉሳችን የተወለዱበት ሥፍራ ነው። እዚያ ኪዳነ ምሕረት ቤተክርስትያን አለች። እዚያ ነው እትብታቸው የተቀበረው» ይላል። እርግጥ ነው ይህን ጉዞ ለማድረግ ቆርጠው የተነሱ ራስ ተፈሪያኖች ጥቂት እንደሆኑ ራስ እዝቄል አይሸሽግም። መኖሪያቸውን ሐረር ያደረጉ ጃማይካውያን እንዳሉም ይናገራል።

«ጉዞው ለኛ ትልቅ ትርጉም አለው። ወደ ሐረር እንድንጓዝ የሚያደርግ መንፈሳዊ ጥሪ ደርሷል። ይህን ጉዞ እኛ ለመጀመር እናስበው እንጂ ጥሪው ለሁሉም የራስ ተፈሪያን እምነት ተከታዮች ነው።»

ራስ ኩማ ሐረር ለራስ ተፈሪ እምነት ተከታዮች ያላትን ሥፍራ ሲያስረዳ፤ «እኔ ሁሉም የራስ ተፈሪ እምነት ተከታይ በሕይወት ዘመኑ አንዴ ኤጀርሳ ጎሮን ቢያይ ደስ ይለኛል። የእስልምና እምነት ተከታዮች ወደ መካ እንደሚያቀኑት ሁሉ የኦርቶዶክስ እምነት ተከታዮች ቤተልሔምን ለማየት እንደሚጓጉት ሁሉ እኛም ሐረርን ማየት እንናፍቃለን» ይላል። ግን ግን የራስ ተፈሪ እምነት ተከታዮች ሐረር ውስጥ እንዴት ያለ ማሕበረሰብ ይሆን ለመመሥረት የሚሹት? ራስ እዝቄል ጉዞው ገና ጅማሮ ላይ ያለ ቢሆንም ልናቋቁም ያሰብነው ማሕበረሰብ ሻሸመኔ ከሚገኘው ለየት ያለ ነው ይላል።

«ለሁሉም የራስ ተፊሪያን እምነት ተከታይ የሚሆን ምቹ ሥፍራ እንዲሆን ነው ፍላጎታችን። እዚያ ከሚኖረው ማሕረበሰብ ተነጥለን የመኖር ዕቅድ የለንም። አንድነትን መሠረቱ ያደረገ፤ እርስ በራስ የሚከባበር እና የሚግባባ ማሕበረሰብ የመፍጠር ፍላጎት አለን።»
ከአርባ ዓመታት በላይ ጃማይካውያንን ያስጠለለችው ሻሸመኔስ ምን ይሰማት ይሆን? ራስ እዝቄል ጉዞው ከሻሸመኔ ጠቅልሎ ወጥቶ ወደ ሐረር የሚደረግ 'ፍልሰት' ተደርጎ እንዳይታሰብ ይሰጋል።

«ጉዳዩ አዲስ ምዕራፍ የመክፈት ጉዳይ ነው። በርካቶቻችን በምዕራብ ሃገራት ተጠልለን የምንኖር ነበርን። አሁን ግን አንድ የሚያደርገንን ነገር እንፈልጋለን። ይህን ስናስብ ደግሞ 'ጃህ' ከተወለዱበት ሥፍራ የተሻለ ቦታ የሚገኝ አይመስለኝም።»

ኤጀርሳ ጎሮ ጉዞው ጅማሬ ላይ ነው ያለው። ኤጀርሳ ጎሮ ላይ አንድ ቤተ - ክርስትያን የማነፅ ሥራ ከዕቅዱ መካከል ይገኛል። በሁለት ዓታት ጊዜ ውስጥ ብዙ ነገሮች ተሳክተው ጉዞ ሻሸመኔ - ሐረር የተሳካ እንደሚሆን ራስ እዝቄል እምነት አለው።

ከሐረሪ ክልል ባህል እና ቱሪዝም ቢሮ ጋር በትብብር እየሠሩ እንደሆነም ይናገራል። የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስትያን የምስራቅ ሐረርጌ ፅህፈት ቤት ጉዞው የተሳካ አንዲሆን ከራስ ተፈሪያኖች ጋር በጥምረት እንዲሰራ እንደሚፈልጉ ራስ እዝቄል ይጠቁማል። በመላው ዓለም የሚገኙ ራስ ተፈሪያኖች ለጉዳዩ ጆሮ መስጠት እንደጀመሩ የሚናገረው ራስ እዝቄል ቤተክርስትያን የማነፁን ሥራ እንዲሁም ሌሎች ተግባራት የሚጠናቀቁ ከሆነ እርዳታው ከዚያም ከዚህም መምጣቱ አይቀርም ባይ ነው።

ኤጀርሳ ጎሮ አዲሲቷ የራስ ተፈሪ እምነት ተከታዮች ትሆን ይሆን? በስተመጨረሻ የእምነቱ ተከታዮች የጃንሆይን የትውልድ ስፍራ መጠጊያቸው አድረርገው ኃይማኖታዊ ጉዟቸውን ወደ ተስፋይቱ ምድር ያደርጉ ይሆን? ።