Tuesday, April 2, 2019

insurance in Ethiopia

በመድን ዘርፉ የተደራሽነትና የአዳዲስ አገልግሎቶች ጥያቄ

የኢትዮጵያ የገንዘብ ተቋማት አጠቃላይ አቅም ከሰሃራ በታች አገሮች አንፃር ሲታይ ብዙ እንደሚቀረው ሲነገር ሲተነተን ቆይቷል፡፡ ዘርፉ ለአገር በቀል ኩባንያዎች ብቻ ክፍት በመደረጉ፣ ከውጭ ለሚመጣበት ውድድር ያልተገባ ከለላ እንደተሰጠው የሚከራከሩ አካላት፣ በተደራሽነቱ ረገድም ዝቅተኛ አፈጻጸም የሚታይበት እንደሆነ ይናገራሉ፡፡

የዘርፉ ባለሙዎችም የተደራሽነቱን ውስንነት ይስማሙበታል፡፡ በባንክም ሆነ በኢንሹራንስ ዘርፉ ያሉት የአገልግሎት ዓይነቶች በጣት የሚቆጠሩ መሆናቸውም ውድድር አልባ መሆኑ የፈጠረው የገበያ መዛባት ተጠቃሚው ማግኘት የሚገባውን አገልግሎት አሳጥቶታል፡፡ በመሆኑም ለዘርፉ መሻሻል ብዙ ለውጥ እንደሚያስፈልግ ይመከራል፡፡ ይዘከራል፡፡

No comments:

Post a Comment