Tuesday, April 2, 2019

ሻንጋይ ከተማ የ5ጂ የቴሌኮም ኔትወርክን በመጠቀም ቀዳሚ ሆነች ።

#የቻይና ከተማ የሆነችው ሻንጋይ የ5ጂ የቴሌኮም #ኔትወርክ #አገልግሎት በመስጠት በአለም ቀዳሚ መሆኗን አስታወቀች፡፡

#ከተማዋ ይህን አዲስ የቴሌኮም ቴክኖሎጂ ይፋ ያደረገችው በሙከራ ደረጃ ነው ተብሏል፡፡
በዚህም ሂደት #ኔትወርኩ ከተማውን ሙሉ ለሙሉ እንዲሸፍን ለማድረግ ባለፉት #ሶስት ወራት ቴክኖሎጂውን #መሸከም የሚችሉ ጣቢያዎች መተከላቸውን ተነግሯል፡፡

#ይህም አዲስ መሰረተ ልማት ቻይና አሜሪካንና ሌሎች #ሀገሮችን በመቅደም ቀጣዮ ትውልድ የሞባይል #ኮሙኒኬሽን ለመፍጠር ምቹ ሁኔታ እንደሚያመቻች ተመልክቷል፡፡

#ቀጣዮ ትውልድ የሞባይል ቴክኖሎጂ እንደሆነ የሚነገርለት የ5ጂ የቴሌኮም #ኔትወርክ ከ4ጂ ቴክኖሎጂ ይልቅ መረጃዎችን #ከኢንተርኔት ከ10 እስከ 100 እጥፍ በሆነ ፍጥነት የማውረድ አቅም አለው፡፡

No comments:

Post a Comment