Tuesday, July 3, 2018

liberalisation & privatization in Ethiopia, ethiopian airlines ወደ ግል ከመዛወሩ በፊት የኤርፖርቶች ድርጅት ከኢትዮጲያ አየር መንገድ ግሩፕ መለያየት አለበት


በደፈናው የልማት ድርጅቶችን ወደ ግል ማዛወር የሚያስከትለው ችግር
ጸሃፊው ስሜነህ ተረፈ
ኢ -ሜይል smofed@gmail.com ወይም
መንግስት በቅርቡ ትላልቅ የመንግስት የልማት ድርቶችን ወደ ግል ለማዛወር መወሰኑ ተሰምቷል ፤ ይህ የፕራይቬታይዜሽን ሂደት መምጣቱ እሰየው ቢሆንም ነገር ግን መንግስት ሊጠነቀቅና ሊያጠናቸው የሚያስፈልጉ ጉዳዮች አሉ ከእነኚህም አንዱ በ2009 ዓ.ም በወጣው የኢትዮጲያ አየር መንገድ ግሩፕ ማቋቋሚያ የሚኒስትሮች ምክር ቤት ደንብ ቁ / 406 ፤ 2009 ዓ.ም መሰረት በተደራጀው የኢትዮጲያ አየር መንገድ ግሩፕ በስሩ የኤርፖርቶች ድርጅትንና እንዲሁም ርካሽ የሰው ሃይልን በመጠቀም በሃገር ውስጥ የአውሮፕላን የተለያዩ አካላትን መፈብረክና መጠገን ለቦይንግና ለኤርባስ ለሌሎችም ኩባንያዎች የምርት አካላት መገጣጠሚያ ማእከልን በባለቤትነት መያዝን የሚያጠቃልል ነው ፤ ኤርፖርቶችን መገንባትና መጠገን፤እንዲሁም ኤሮኒተካል አገልግሎቶችንና ኤሮኖቲካል ያልሆኑ አገልግሎቶችን መስጠት ለኤር ኦፕሬተሮች የሚሰጡ አገልግሎቶችን መስጠት፤ የአቪየሽን ባለሙያዎችን ማሰልጠንን ቀድሞ በኤርፖርቶች ድርጅት እና በሲቪል አቪየሽን ባለስልጣን ይሰሩ የነበሩ ስራዎች ሁሉ ለአየር መንገድ ግሩፕ ተሰጥተዋል በዚህ ደንብ መሰረት የግሩፑ የተከፈለ ካፒታል 31.2 ቢሊየን በር ሲሆን የተፈቀደው ካፒታል ደግሞ 100 ቢሊየን መሆኑ ተገልጧል፡፡
 በመጀመሪያ የኢትዮጲያ አየር መንገድ የአየር ትራንስፖርት ሰጪ ድርጅት እንደመሆኑና ኤርፖርቶችን ማስተዳደርና መገንባት፤ ማስፋፋት፤መጠገን ፤ የአየር ትራፊክን መቆጣጠር እና የአውሮፕላን አካላትን መገጣጠም ስራ በሃገር ውስጥ መሰራት መጀመሩ መልካም ቢሆንም ራሱን የቻለ ድርጅት ሆኖ መቋቋም የነበረበት ነው እንጂ የአየር ትራንስፖርትን አገልግሎት የሚሰጠው አየር መንገድ እዚህ ውስጥ መግባት አልነበረበትም ፡፡ የምእራቡ ዓለም ታላላቅ ኩባንያዎች ኮር ቢዝነስ (Core Business) ማለትም የኩባንያው ዋነኛ ስራውና ዋናው የገቢ ምንጩ ከሆነውና በርካታ ባለሙያዎችና ልምድ፤ እውቀት ካለው ዘርፍ ማለትም የማጓጓዝ አገልግሎት ዘርፍ መውጣት አልነበረበትም ፡፡ ከዋናው ቢዝነስ የሚወጡ ኩባንያዎች የእነሱ ዋነኛ ሙያ ወዳልሆነው ዘርፍ በሚቀላቀሉበት ወቅት ለከፍተኛ ወጪና ኪሳራ የሚዳረጉ ሲሆን ዋናው ስራቸው ያልሆኑትን በማራገፍ ወደ ዋናው ስራቸው ሲመለሱ ተስተውሏል ፤ ዘርፉ ውድድር ያለበት እንደመሆኑ ትኩረቱ መሆን ያለበት በትራንስፖርት ዘርፍ ነው ፤ በዚህ ደንብ መሰረት አየር መንገዱ በሆቴልና ቱሪዝም ዘርፍ መሰማራቱና በሌሎች አየር መንገዶች ድርሻ መግዛቱ፤ቦንድ መሸጡ ያጠናክረዋል ከዚህ ውጭ ግን የሁለቱን ድርጅቶችን የስራ ድርሻን መጠቅለሉ ግን ተገቢ አይደለም ፡፡
በ2009 ዓ.ም በወጣው አዋጅ መሰረት ግን እነዚህን 3 የተለያዩ ድርጅቶች ይሰሩት የነበረውን ስራ የኢትዮጲያ አየር መንገድ ግሩፕ የሚል ስያሜ ከተሰጠው ድርጅት ጋር አለአግባብ የተቀላቀሉ ሲሆን የአየር ክልል ተቆጣጣሪ የሆነውን እንዲሁም ኤርፖርቶችን ከኤርፖርቶች ድርጅት ተከራይቶ የሚጠቀመው የኢትዮጲያ አየር መንገድን ከኤርፖርቶች ድርጅት ጋር ተቀላቅሏል ፡፡ ነገር ግን የኤርፖርቶ ድርጅት ኤርፖርቶችንና ተርሚናሎችን የሚሰራ ፤ የሚጠግንና የአየር ማረፊያ ሜዳዎችን ለአየር መንገዶች በማከራየት በርካታ ቢሊየን ብሮችን በየአመቱ ለመንግስት ገቢ የሚያደርግ ነው፡፡ ድርጅቱ የኮቴ በማስከፈል ገቢን የሚያኝ ሲሆን ፤ ከዚህም በተጨማሪ ወደ ሃገር ውስጥ የሚገቡና የሚወጡትን ደህንነትን መቆጣጠር ፤ መፈተሽ የመሳሰሉትን የደህንነት ስራዎችን የሚሰራ ነው ፡፡
ከዚህም በተጨማሪ በአየር ማረፊያ ግቢ ውስጥ ያሉ ሱቆችን ቢሮዎችንና የመኪና ማቆሚያዎችን በማከራየት እንዲሁ ለመንግስት ገቢን የሚያስገባ ሲሆን ሲጀመር ከኢትዮጲያ አየር መንገድ የተለየ በመሆኑ ከአየር መንገዱ ጋር መቀላቀል አልነበረበትም ፤ አየር መንገዱን ለማሳደግ ከተፈለገ እንኳን አሁን እንደወጣው ፖሊሲ የተወሰነ ድርሻን ወደ ግል ባለሃብቶች ማዛወር እንጂ መቼም ቢሆን የአገሪቷ ንብረት የሆኑትን ኤርፖርቶችን በማቀላቀል መሆን አልነበረበትም፡፡ ይህ የተለያየ አደረጃጀት ስራውንም የተለያየ በመሆኑ ሲሆን በቅርቡ በወጣው አዋጅ ግን ተቀላቅለዋል ውህደቱ በተፈጸመበት ወቅት የኢትዮጲያ አየር መንገድ ዋና ስራ አስፈጻሚ እንደገለፁት ይህ ውህደት ወደ ኢትዮጲያ አቪየሽን ግሩፕ ወደ ሚባል የአቪየሽን መስሪያ ቤትንም ጨምሮ አንድ እንደሚሆን ገልጸዋል፡፡
ነገር ግን የእነኚህ 3 ወሳኝ የሆኑ ነገር ግን የተለያየ ስራን የሚሰሩ ድርጅቶችን ከተዋሃዱ በኋላ የአየር ደህንነትንና የአውሮፕላኖችን አስተማማኝነትን የፓይለቶችን የሙያ ፈቃድ የሚሰጠው፤ የሚፈትሸውና ፈቃድን የሚሰጠው የሚቆጣጠረው የአቪየሽን መስሪያ ቤትና ስትራቴጂያዊ የሆኑትን የአውሮፕላን ማሳረፊያ ሜዳዎችን በንብረትነት የያዘው ተቋምን የኤርፖርቶች ድርጅትን ጨምሮ ወደ ግል ማዛወር ከሃገሪቱን ደህንነት ጭምር አደጋ ውስጥ የሚከት ነው ፤እንኳን ለውጭ ባለሃብት ቀርቶ ለሃገር ውስጥ ባለሃብትም እሚሰጥ አይደለም ፡፡ ኢትዮጲያ አየር መንገድን ከአውሮፕላኖቹና ከቁሳቁሶቹ ጋር ብቻ በመለየት ወደ ግል ማዛወር የሚቻል ሲሆን ወደ ግል የማዛወር ሂደቱ ከመጀመሩ በፊት በመላ ሃገሪቱ በርካታ የአውሮፕላን ማረፊያ ሜዳ ባለቤት የሆነው የኤርፖርቶች ድርጅት ተለይቶ መውጣት አለበት ፡፡   
አየር መንገዱ ወደ ግል ይዛወራል መባሉ አየር መንገዱን ያተጋው ይመስላል ፤ በዚህም መሰረት ፤ለረጅም ግዜ ያስራ ተቀምጠው የነበሩ በሞተር ችግር የማይሰሩ ሞተሮችን ማስነሳትና ወደ ስራ እንዲጀመር ማድረጉ ተዘግቧል ፡፡ ሪፖርተር ጋዜጣ እንደዘገበው ‹‹የኢትዮጵያ አየር መንገድ የሮልስ ሮይስ ሞተሮች የተገጣጠሙላቸው አራት ቦይንግ 787-8 አውሮፕላኖች ካለፈው ሚያዝያ ወር ጀምሮ ቆመው የነበሩ ቢሆንም፣ ከሞተር አምራቹ ኩባንያ ጋር በመነጋገር ሞተሮቹ እየተጠገኑ አውሮፕላኖቹ ወደ ሥራ በመመለስ ላይ እንዳሉ ሲገለፅ አየር መንገዱ ለቆሙት አውሮፕላኖች ካሳ እየተከፈለው መሆኑን ገልጿል››፡፡ የሁለቱ ድርጅቶች መቀላቀል ለሙስና ሰፊ በርን የከፈተ መሆኑ፤የር መንገዱ ግልጽ ባልሆነ መንገድ የገዛቸውን አውሮፕላኖችን መልሶ መሸጡ እንደገና መልሶ የሸጣቸውን አውሮፕላኖችን እንደሚከራይ ፤ የሰራተኛ አያያዙ ችግር እንዳለበት፤ እንዲሁም የስራ ቅጥርና ዝውውርን በተመለከተ የዘመዳማቾች ቤት ነው ተብሎ በሰፊው የሚተች ተቋም መሆኑ ይታወቃል ፡፡ 
የኢትዮጲያ መብራት ሃይል ቢሆን ባለፈው አመት ብቻ 128 ሚሊዮን ዶላር ለሃገሪቱ ያስገባ ሲሆን ይኀው ለጎረቤት ሃገራት መብራትን መሸጥ አትራፊና የውጭ ምንዛሬን የሚያስገኝ ሲሆን በሃገር ውስጥ የኤሌክትሪክ ስርጭትንና ማከፋፈልን ለማሻሻል ሲሆን የሃገር ውስጥም ሆነ የውጭ ባለሃብቶች ቢገቡበት የአገልግሎት አሰጣጡን የሚያሻሽለው ሲሆን ነገር ግን ወደ ውጭ የሚላከውና ለሀገሪቱ የውጭ ምንዛሬን የሚያስገኘው ዘርፍ ግን በመንግስት እጅ ሆኖ ቢቆይ የሚያስገኘው ጠቀሜታ መታየት አለበት፡፡ በእርግጥ ሃይልን በማሰራጨትና በማከፋፈል ላይ በግል ባለሃብቶች መግባታቸው እንደ ኢትዮጲያ ላለ ትልቅ ሃገር አስፈላጊ መሆኑን ጠ/ሚሩ ገልፀዋል፡፡ የተመረተ ሃይል እያለ ነገር ግን በስርጭትና በማከፋፈል ሂደት ሃይል በተደጋጋሚ እየተቆራረጠ መሆኑና በኢኮኖሚው ላይ በተለይም በማምረትና በከተሞች አካባቢ በአገልግሎት ዘርፍ ላይ ጉዳትን እያደረሰ መሆኑን መረዳት ይቻላል፡፡ ማንኛውም ሰው እንደሚገምተው የግል ባለሃብቶች  በመብራት ማከፋፈልም ሆነ ማሰራጨት ዘርፍ ሲሰማሩ አሁን ያለው ርካሽ የሃይል አቅርቦት አይኖርም ነገር ግን የሃይል መቆራረጡ ይቀንሳል ዋጋ ግን ወደድ ይላል ይህን ለህብረተሰቤ ግልፅ በማድረግ ይጠበቃል፤ በርካታ ትላልቅ የመንግስት ድርጅቶች ወደ ግል ወደ የተዛወሩባቸው ሃገራት የዋጋ መጨመር በስፋት ታይቷል፡፡
ኢትዮ ቴሌኮም ቀድሞ የመገናኛናት ትራንስፖርት ሚ/ር ጋር የተቀላቀለና በከተማው ውስጥ ያሉ የመንግስት ህንጻዎችንና ሰፋፊ መሬቶችን የያዘ ስለሆነ እነኚህን የሃገር ንብረቶችን ከቴሌኮሙ ቁሳቁሶች መለየትና ቴሌን ከነቁሳቁሱ ማዛወርና የሃገር ሃብት የሆኑት ህንጻዎችን ግን ወደ መንግስት ንብረትነት መቀላቀል ያስፈልጋል ፡፡ ይህ ብቻ አይደለም የድርጅቶቹን ሃብትና እዳ መግለጫ ለማዘጋጀት እንዲሁም በትክክል ድርጅቶቹ በገበያው ምን ያህል እንደሚያወጡ ‹ማርኬት ካፒታላይዜሽን› ምን ያህል እንደሆነ በገለልተኛ ኦዲተሮች ማዘጋጀት ራሱ እስከ አንድ አመት ድረስ ሊፈጅ የሚችል ነው፡፡
ከዚህም በተጨማሪ ወደ ግል የማዛወሩ ሂደት ለግዜው የሃገሪቱን የውጭ ምንዛሬ እጥረትን ለማቃለልና የገንዘብ እጥረትን ለማቃለል ቢረዳም ውሎ አድሮ ግን በሚገኘው ገቢ ሌላ አቅምን የሚፈጥር እንዲሆን ማድረግ ያሻል፡፡

Tuesday, June 12, 2018

liberalism Ethiopia ethiopian Airline ethio Tel



ከፈረሱ ጋሪው የቀደመው የልማት ድርጅቶን ወደ ግል የማዛወርየ‹‹ሊበራሊዝም››ሂደት

በአሁኑ ሰአት ኢህአዴግ መራሹ መንግስት ዋና ዋና የሆኑትን የመንግስት የልማት ድርጅቶችን በከፊል ወይም ሙሉ ለሙሉ ወደ ግል ለማዛወር መወሰኑ ከዚህ ቀደም ገዢው ፓርቲ ያራምድ ከነበረው የተለየ አቋም ሲሆን እነኚህ የልማት ድርጅቶች ወደ ግል አይዛወሩም በሚል በነሱ አትምጡብኝ የኒኦ ሊበራል ሃይሎች አመለካከት ነው ይሄንን አንቀበልም ሲል የቆየ ቢሆንም አሁን ግን ብዙዎቹን ምእራባውያኑን ጭምር ያስገረመ የፖሊሲ ለውጥን አድርጓል፡፡ የፖሊሲ ለውጡ ያልተጠበቀ ሲሆን የዘገየና ትንሽ(Too little, Too Late)ፈረንጆቹ እንደሚሉት ነው፤ ከዚህ በተጨማሪ ግን የዚህን ያህል ግዙፍ የፖሊሲ ለውጥን ለማድረግ ከመነሳት በፊት ኩባንያዎቹን ለማስተላለፍና ለውጡን መምራት በህዝብ ዘንድ ተአማኒ በሆነ ሁኔታ ሽግግር እንዲደረግ አስፈላጊ የሆኑት ቅድመ ሁኔታዎች መሟላት ነበረባቸው ፡፡
በማንኛውም ሃገር እንደሚደረገው ሁሉ አንድን ተቋም ወደ ግል ለማዛወር እንዲሁም አክስዮኖችን ለህዝብ ለመሸጥ አስቀድሞ የሚያስፈልጉ መዘጋጀት ያለባቸው መደላድል የሚሆኑየገበያ መሰረተ ልማቶች፤ደጋፊ የህግ ማእቅፎችና ተቋማት የሚያስፈልጉ ሲሆን ለምሳሌ ስለ አክስዮን ድርጅቶች የሚደነግገውናከ60 አመት በፊት የወጣው የንግድ ህግ ይሻሻላል ቢባልም ተሻሽሎ አልወጣም ፤ ከዚህ ቀደም ትላልቆቹ የመንግስት ድርጅቶች የቢራ ፋብሪካዎቹን ጨምሮ በዝግ ጨረታ ላሸነፉት የውጭ ኩባንያዎች የተሸጡ ሲሆን ይፋዊ የሆነ የአክስዮን ገበያ ባለመኖሩ ምክንያትእስካሁን ድረስ መንግስት ትላልቆቹን ድርጅቶቹን የመግዛት እድልን ያገኙት የውጭ ባለሃብቶችና እንደ ሚድሮክ ያሉት ናቸው ፡፡እነኚህ ድርጅቶች አክስዮኖቻቸው ለህዝብ ይሸጣሉ ቢባልም በየትኛው የአክስዮን መገበያያ መድረክ እንደሆነ ግልፅ አይደለም ፤ በተደጋጋሚ የንግዱ ህብረተሰብ የአክስዮን ገበያ እንዲከፈት ውትወታ ቢያደርግም በመንግስት በኩል ግን መቆጣጠር አንችልም ፤ ሃገሪቱ ለዚህ ዝግጁ አይደለችም ….ወዘተ በሚሉ ምክንያቶች ፈቃደኝነት አልታየም ፤ ኢትዮጲያ የአክስዮን ገበያ ከሌላቸው በዓለም ላይ ካሉ 40 አገራት ትልቋ መሆኗ የዓለም ሚዲያዎች የዘገቡት ጉዳይ ነው ፤የአሁኑን የመንግስት ድርጅቶችን ለህዝብ አክስዮን እሸጣለሁ የሚለው አቋም በመጀመሪያ የአክስዮን ገበያና ግልፅ የሆኑ የአክስዮን ኩባንያ ድንጋጌዎችና ፤ የንግድ ህግጋት በሌሉበት አክስዮኖቹ እንዴት እንደሚሸጡ ግልፅ ማድረግ ይጠበቃል ፡፡
በመግለጫው ላይ እንደተጠቀሰው ወደ ግል በሚዛወሩበት ሙስናን ለመከላከልጥንቃቄን እንደሚደረግ አመልክቷል፡፡በቀድሞዋ ሶቭየት ህብረት አባል በሆኑበት ሃገራትና በአሁኗ ራሺያ በቦሪስ የልሲን ዘመን የመንግስት ድርጅቶችን ወደ ግል በሚያዛውሩበት ወቅት ከፍተኛ ሙስና በመፈፀሙ ዋና ዋና የሚባሉ ድርጅቶች በግለሰቦች እጅ ገብተው አሁን ቱጃር ኦሊጋርክ የሚባሉት የሃገሪቱን የሀብት ሃብት ምንጭ የሆኑትን ኩባንያዎች በርካሽ ዋጋ በእጃቸው ሊያስገቡ በቅተዋል በዚህም ሩስያና ፤ እንደ ኡክሬን ያሉ ሃገራት በሃብታሙና በደሃው መሀከል ሰፊ የሆነ የሃብት ልዩነት ከሚታይባቸው የዓለም ሃገራት ተርታ ተሰልፈዋል ፤ ብዙዎቹ የአሁኑ የሩስያና ኡክሬይን ቢሊየነሮችም በዚህ መንገድ ሃብትን ያካበቱና ፖለቲካውንና ኢኮኖሚውን ለመቆጣጠር በቻሉ ሰዎች ስለሆነ ዲሞክራሲን ለማስፈንም እንቅፋት ሆኗል ፤ የአሁኑ የሩስያ ፕሬዝደንት ፑቲንም በእነኚህ ዲታ ኦሊጋርኮች ጋር በመሻረክና የሃገሪቱን የተፈጥሮ ሃብት በመከፋፈል ሃገሪቱን እየገዙ እንዳለ ይታወቃል፤እነኚህ ባለሃብቶችም ሃገራቸውን ስለማያምኑ ኑሯቸውን በአውሮፓና እንግሊዝ ሲያደርጉ የሃገራቸውን ሃብትም ወደ ውጭ በማሸሽ ኪሳራን ተከትሎም የተዛባ የሃብት ክፍፍል አስከትለዋል፤ እንዲሁም በቻይናም የመንግስትን ኩባንያዎችን እንደ ሩስያ አይሁን እንጂ የኮሚኒስት ፓርቲው አባላትና ዘመዶች ሊከፋፈሏቸው በቅተዋል፡፡
ውሳኔው በገዢው ፓርቲ የተወሰነ ሲሆን ነገር ግን ይህ ቁልፍ ውሳኔ እንደመሆኑ መጠን መወሰን የነበረበት በፓርቲ መዋቅር ነው ወይንስ አስፈጻሚ በሆነው በሚኒስትሮች ም/ቤትና በህግ አውጪው መፅደቅ ነው የነበረበት የሚለው አነጋጋሪ ነው ፤ ጉዳዩ ወደ ፓርላማ ሄዶ ህግ ሆኖ በሚቀየርበት ወቅት ፓርላማው የገዢውን ፓርቲ ውሳኔ ማፅደቅ ይጠበቅበታል ማለት ነው ፡፡ትላልቅና ወሳኝ የሆኑ የኢኮኖሚ አውታር የሆኑ ድርጅቶችን ፤ወደ ግል የማዛወር ሂደት በጥንቃቄ መተግበር ሲኖርበት ከላይ የተጠቀሱትንና የሌሎችን ሃገራትን ልምድን ማስተዋል ያሻል፤ይዛወራሉ ከሚባሉት መሃከል ቴሌን ብንወስድ ለውጭ ባለሃብቶች ክፍት ከመደረጉ በፊት ለሃገር ውስጥ ባለሃብቶች ክፍት ተደርጎ የሃገር ውስጥ ባለሃብቶች ሃብትን እንዲፈጥሩበትና የመወዳደር ብቃታቸውን ለማሳደግ ቅድሚያ እድል ማግኘት የሚገባቸው ሲሆን እነሱ ሲጠነክሩ ለውጭዎች ክፍት መደረግ የነበረበት ቢሆንም ለረጅም አመታት ለሃገር ውስጥ ባለሃብቶች ጭምር ክፍት አይደረግም በሚል ግትር አቋም በመንግስት ሞኖፖሊ ለአመታት ተይዞ ቆይቷል፤ የአየር መንግዱም ዘርፍ ከአነስተኛ አውሮፕላንና ከአምቡላንስና ሄሊኮፕተር በስተቀር ለትላልቅ የግል አየር መንገዶች ፈቃድ የማይሰጥ ሲሆን መጀመሪያ ዘርፉን ክፍት በማድረግ የሃገር ውስጥ ትላልቅ አውሮፕላኖችን ለሚያንቀሳቅሱ ክፍት መደረግ ነበረበት ፡፡ አሁን ክፍት ይደረጋሉ የሚባሉት ዘርፎች በሙሉ የሃገር ውስጥ ባለሃብቶች ያለ ገደብ እንዲንቀሳቀሱ ቢፈቀድ ስንት ቴሌና ስንት ትላልቅ የግል አየር መንገዶች ሊኖሩ እንደሚችሉ መገመት ይቻላል፡፡
የፋይናንሱን ዘርፍ ብንመለከት የግል ኢንሹራንሶችና ባንኮች መጀመሪያ ለሃገር ውስጥ ተወዳዳሪዎች ክፍት የተደረገ ሲሆን አንዳንዶቹ ተቋማት ከፍተኛ ካፒታልን እስከመፍጠር ደርሰዋል አሁን የዚህ ዘርፍ ችግር ለሃገር ውስጥ ባለሃብቶች ብቻ ክፍት መሆኑና ለውጭ ባለሃብቶች ክፍት አለመደረጉና ለረጅም ግዜ ዝግ ሆኖ መቆየቱ ደግሞ በዘርፉ በቂ ውድድር እንዳይኖርና የውጭ ምንዛሬን ለማፍራት በራሱ እየፈጠረ ያለው ችግር አለ፡፡ ነገር ግን አሁን ክፍት ይደረጋሉ የተባሉት ዘርፎች ቅደምተከተሉ መሆን ያለበት መጀመሪያ ለሃገር ውስጥ ባለሃብቶች እንዲሳተፉ ህጎችን ማውጣት የነበረበት ሲሆን በመቀጠልም በሃገር ውስጥ ካፒታልን ከፈጠሩና ከውጭ ባለሃብቶች ጋር መወዳደር የሚያስችል አቅምን በሚፈጥሩበት ወቅት የውጭዎቹ እንዲገቡ ይደረጋል፤ ነገር ግን የአሁኑን ለየት የሚያደርገው ግን ለውጭም ለሃገር ውስጥም እኩል ክፍት ማድረጉ የተለየ ያደርገዋል ፡፡በኢትዮጲያ የመንግስት ድርጅቶችን ወደ ግል የማዛወር ሂደት ግልፅነት የጎደለውና ለሙስና የተጋለጠ ሲሆን ፤ ብዙዎቹ ትላልቆቹ ለውጭ ባለሃብት የተላለፉ ሲሆን ህብረተሰቡ ከደመወዝተኝነት ውጪ ሌላ ሃብትና ንብረትን እንዳያፈራ ሲያደርገው ከእነዚህ ድርጅቶች ውስጥ የባለቤትነት ድርሻ መብት ለመግዛት ምንም እድልን ሳያገኝ የቀረ ሲሆን የአሁኑ ለየት የሚያደርገው ግን ለህዝቡም ድርሻን እሸጣለሁ ማለቱ ነው ይህ መልካም ሲሆን ህዝቡም ተሳታፊ መሆኑ ለግልፅነት አጋዥ ነው፡፡
የገንዘብና / ኢኮኖሚ / ትብብር ሚ/ሩ 59 ቢሊየን ብር በላይ የ2011 ዓ.ም. በጀት ጉደለት ማሳየቱንና ይህንንም ለመሙላት በሃገር ውስጥ የገንዘብ ህትመት ይሸፈናል ማለታው መጪው ግዜ የባሰ የዋጋ ግሽበት የሚታይበትና የዜጎች ኑሮ የበለጠ ፈታኝ ሁኔታ ውስጥ እንደሚገባ አመላካች ነው፡፡ የበጀት ጉድለቱን ለመሙላት አሁን ካለው አሳሳቢ ከሆነውና አሁንም እየናረ ካለው የዋጋ ግሽበት አንጻር እንደ ከዚህ ቀደም ተጨማሪ ገንዘብን ወደ ኢኮኖሚው ቢለቀቅ የሚፈጥረውን ተጨማሪ ግሽበትን መቋቋም ስለማይቻል እነኚህን ድርጅቶችን መሸጥ አማራጭ የሌለው ሆኖ ተገኝቷል
እንደ ቻይና ያሉ ሃገራትም በተነሳው ብጥብጥና የፖለቲካ አለመረጋጋት ሳቢያ ወደዚህ የሚልኩትን ኢንቨስትመንታቸውን ያዝ ማድረጋቸውም ተሰምቷል ፤ ከውጭ ይገኝ የነበረው ብድር የመቀነስ አዝማሚያን አሳይቷል - በመሸጥ ካልሆነ በቀር እንደ ከዚህ ቀደሙ በብድርም ሆነ በእርዳታ በቀላሉ ከውጪ ገንዘብ ማግኘት እንደማይቻል መገመት ይቻላል ፤ስለሆነም መንግስት ካለበት የእዳ ጫናና ከከፍተኛ የበጀት ጉድለት ለማቃለል የእነዚህን ድርጅቶችን ሽያጭ እንዳሰበው መገመት ይቻላል ፤ በሌላ በኩል ደግሞ ኢኮኖሚውን ለውጭ ባለሃብቶች ሊበራላይዝ›› ክፍት አድርግ የሚለውን የምእራባውያንን ግፊት መልስ ለመስጠትና የፖሊሲ ማሻሻያን በማድረግ ሊመጣ የሚችልን እርዳታንና ብድር ለማግኘት ሊሆን ይችላል ፡፡ ሃገሪቱ የዓለም የንግድ ድርጅት አባል እንዳትሆን አንድ እንቅፋት ሆኖ የቆየው ይሄው ክፍት አይደረጉም የሚባሉት ዘርፎች ጉዳይ ነው ፤ ይሁንና ወደ ግል ይዛወሩ በተለይም ለሃገር ውስጥ ባለሃብቶች ይተላለፉ መባሉ መልካም ቢሆንም ያለውን የሃብት ልዩነትን እንዳያሰፋውና ለማስተካከል በሚያስቸግር ሁኔታ ሃብት በጥቂቶች እጅ መከማቸትን እንዳይፈጥር ጥንቃቄን ማድረግ ያሻል፡፡የልማት ድርጅቶቹ ለረጅም አመታት ሞኖፖሊ በመሆን ባለሃብት አይገባባቸውም መባላቸው በሃገሪቱ እድገት ላይ የራሱን አሉታዊ ተፅእኖን ፈጥሮ ቆይቷል ፤ ቴሌና አየር መንገድ ድርጅቶች በጣም አትራፊ ስለሆኑ እንደ ኢትዮጲያ አየር መንገድ ያለው በውጭ ምንዛሬ ስለሆነ በተለይም የውጭ ባለሃብቶቹ ትርፋቸውን ወደ ውጭ ማውጣትም ይችላልበዚህም ምክንያት የውጭ ባለሃብቶችን ለመሳብ ያስችላል ፤ ነገር ግን ከቴሌ በተለየ ሁኔታ አየር መንገዱ አትራፊና የብሄራዊ መለያ እንደመሆኑ መጠን እርሱን ወደ ግል ማዛወሩ የተቻኮለ ውሳኔ ነው፡፡
በሌላ በኩል ደግሞ እነኚህ የልማት ድርጅቶች በሙስናና ውጤታማ ያልሆነን አገልግሎት በመስጠት የሚታወቁ ናቸው እንደ ቴሌ ፤ (Shipping Lines) ሺፒንግ ላይንስ ያሉት መንግስታዊ ሞኖፖሊዎች ሲሆን ተወዳዳሪ ኩባንያዎች ቢኖሩ የዋጋና የጥራት ልዩነት ሊመጣ የሚችል ሲሆን ለዚህ የገበያ ውድድር መልካም እድልን ይፈጥራል ፤ከእነኚህ ኩባንያዎች ግልጽ የሆነ የሂሳብ አያያዝ የሚጠይቅ ሲሆን የሂሳብ ሪፖርቶችንም በየሩብ አመቱ በግልፅ ማተምን ይጠይቃል፡፡ ከዚህ ቀደም ለኢትዮያ ዋነኛ አበዳሪ የሆነችው ቻይና የንግድ መርክብ ድርጅት ውስጥ ድርሻ ይሰጠኝ ብላ ጠይቃ የነበረ ሲሆን ለውጭ ባለሃብቶች ክፍት ሲደረግ ቻይናና ሌሎች የሩቅ ምስራቅ አበዳሪዎች ኢኮኖሚውን ለመቆጣጠር የሚስችላቸውን ድርሻ ሊይዙ ይችላሉ የሚል ስጋት አለ፡፡ መንግስት አብዛኛውን ድርሻ አሁንም ቢሆን እኔ እይዛለሁ ቢልም በሂደት ግን አንዴ መሸጥ ከጀመረ እየሸጠ መውጣቱ የማይቀርና የግል ባለሃብቶቹ ድርሻ እያየለ መምጣቱ አይቀርም ስለዚህ ቋሚ የሆነ የአክስዮን ግብይት በማቋቋም ማንኛውም ሰው ባለው አቅም አክስዮኖችን የመግዛት እድልን ማግኘት አለበት፡፡
የወጪ ንግድ ገቢ የሃገሪቱን ምንዛሬ ፍላጎትን ማሟላት ባቃተው ወቅት ድርጅቶቹን የተወሰነውን ድርሻ መሸጥ እንደ አንድ የገቢ ምንጭ ሆኖ ሊያገለግል ቢችልም በዘላቂነት ግን በሽያጩ ከሚገኘው ገቢ አስተማማኝ ገቢን የሚያስገኝ አቅምን መፍጠር ዋነኛ ተግባር መሆን አለበት፡፡የኢኮኖሚ ማሻሻያ ለውጡ በዚህ መገታት የሌለበት ሲሆን የሃገሪቱን ሃብት ለረጅም ዘመናት አስረው የያዙና ትርፋማ ያልሆኑ ዘርፎች ለውድድር ክፍት በማድረግ በተሻለ ሁኔታ በግል ባለሃብቶች እንዲተዳደር መደረግ አለበት ፡፡
 

Tuesday, May 22, 2018

የፖሊሲማሻሻያንየማድረግአስፈላጊነትናየመንግስትዝግጁአለመሆን

የሃገራችንን ምጣኔ ሃብት በተከታታይ አመታት እድገትን እያስመዘገበ የቀጠለ ሲሆን ኢኮኖሚውአሁንባለበትሁኔታእድገቱንለማስቀጠልግንየምጣኔሃብትናማሻሻያንማድረግይጠበቅበታል ፡፡አንድምጣኔ - ሃብት አንድ የእድገትደረጃላይሲደርስከዚያእድገትጋርእሚመጣጠንየፖሊሲማሻሻያዎችንይፈልጋል ፡፡ ለምሳሌቻይናኢኮኖሚዋ እያደገና እየዘመነ (ማቹር) ሲደርግተከታታይየሆኑማሻሻያዎችንእያደረገችትገኛለች ፡፡በተለይምየፋይናንሱ ዘርፍ የዚህ አይነት ማሻሻያዎችን የሚፈልግ ሲሆን እስከ ቴሌኮም ዘርፉ ድረስ የዚህን ዓይነትማሻሻያዎችካልተደረጉለትቀጣዩየኢኮኖሚእድገትባለበትየመቆምባህሪንያሳያል ፡፡ከዚህም በተጨማሪ ከውጭ የሚመጣቀጥተኛኢንቨስትመንትእያደገመሄድአለበትእንደኢትዮጲያላለበርከትያለየውጭምንዛሪንየሚያስገኝአቅምንገናያልፈጠረ ኢኮኖሚየውጭባለሃብቶችበኢኮኖሚውውስጥበሰፊውተሳትፎማድረጋቸውአስፈላጊነው ፡፡
        በሌላበኩልደግሞመንግስትበጣምወሳኝከሆኑትዘርፎችውጭያሉትወደግልመዛወርያባቸውሲሆንበአብዛኛውበመንግስትስር የሚገኙት የልማት ድርጅቶች የግል ባለሃብቶች እጅ ሆነው ሊቀጥሉ የሚችሉ ናቸው፤ እነኚህን ድርጅቶች ወደ ግል ማዛወር አንድ አማራጭ ሲሆን፤ ነገር ግን ኢህአዴግ መራሹ መንግስትመጀመሪያካደረጋቸውለውጦችወዲህለቀቅየለየኢኮኖሚማሻሻያንለማድረግተነሳሽነትንሲያሳይአይታይም ፡፡ ኢህአዴግ በጣም የሚያደንቃትቻይናበርካታደፋርየሆኑማሻሻያዎችንእያደረገችሲሆንበተለይምበፋይናንስእናበቴሌውዘርፍቀላልየማይባሉለውጦችንአድርጋለችበዚህምየዓለምየንግድድርጅትአባልለመሆንየቻለችሲሆንበዚህምእጅግተጠቃሚሆናለች ፤በኢንዱስትሪምርቶቿሰፊየሆነየዓለምገበያንለመቆጣጠርበቅታለች ፡፡ ገዢውፓርቲኢህአዴግግንዓለምየንግድድርጅትአባልለመሆንየሚያስፈልገውንምጣኔሃብታዊማሻሻያዎችንለማድረግምንያህልፈቃደኛእንደሆነአይታውቅም ፡፡
በተለይምግልፅነትንለመፍጠርሲባልእንደአክስዮንገበያየመሳሰሉትንለመክፈትናካፒታልንእንዲሁምየቦንድገበያንበመክፈትእዚሁካለየሃገርውስጥየፋይናንስምንጭለማሰባሰብእድልንየሚፈጥርየነበረቢሆንምበሃገርውስጥኩባንያዎችስራዎቻቸውንለማስፋፋትየሚያስፈልጋቸውንካፒታልበቀላሉለማሰባሰብያለውንእድልአጥብቦታል ፡፡ለፋይናንስአቅርቦት በውጭ ብድር ላይ ሙሉ ለሙሉ ከመመስረት ይልቅ የሃገር ውስጥ ፋይናንስን ለማሰባሰብ  እድልን ይፈጥር የነበረ ቢሆንም በዚህ ዘርፍ ይህ ነው የሚባል ለውጥ ሳይደረግ ቀርቷል ፡፡ የውጭ ባለሃብቶችም በቀላሉወደሃገሪቱኢንቨስትአድርገውበሚፈልጉበት ወቅት ገንዘባቸውን መልሰው እሚያወጡበት እድልአለመኖሩናያለአክስዮንገበያበቀጥተኛኢንቨስትመንትብቻእንዲሳተፉመፈለጉበተለይምበኤክስፖርትዘርፍንለማሳደግበሚያስችልመልኩበሚፈለገውደረጃየውጭባለሃብቶችንበማምጣትአልተቻለም ፡፡
        መንግስትበትላልቅየመሰረተልማትግንባታዎችመሳተፉመልካምቢሆንምእነኚህፕሮጀክቶችእንደመሆናቸውበረጅምግዜግንየኢኮኖሚውንመሪነትመያዝያለበትየግሉዘርፍነውፕሮጀክቶችየስራግዜውያቸውንሲጨርሱየሚጠናቀቁእንደመሆናቸውመጠንከፍተኛየመንግስትወጪንማውጣትብቻኢኮኖሚውንለመምራትአዳጋችሲሆንእንደዚሁምለእነኚህትላልቅፕሮጀክቶችየሚያስፈልገውንገንዘብለማሟላትሃገሪቱንእዳውስጥየመንግስትንእዳእያናረውየሚሄድእንደመሆኑኢኮኖሚውንለመምራትየግሉክፍለኢኮኖሚየበለጠሚናንመጫወትያለበትስርአትመዘርጋትአለበት ፡፡ትላልቅፕሮጀክቶችለኢትዮጲያአስፈላጊመሆኑየታወቀሲሆንኢኮኖሚውንበማነቃቃትበኩልከፍተኛሚናንእንዳለውማንምየሚረዳውነው ፡፡
በምእራቡአለምየኢኮኖሚመቀዛቀዝበሚኖርበትወቅትምጣኔሃብቱንለማነቃቃትመንግስትትላልቅፕሮጀክቶችንበመስራትበዚያውምኢኮኖሚውንበማነቃቃትየስራእድልንበመፍጠር፤ገንዘብእንዲሽከረከርናወዲውምከገቡነበትሪሴሽንለመውጣትየሚጠቀሙበትየኬኒዥያንምጣኔሃብትአዋቂዎችየሚመክሩትና በ1930ዎቹ በሩዝቬልትእንዲሁም በ2008 ዓ.ምበነበረውየአሜሪካንሪሰሽንበኦባማአስተዳደደርዘመንተግባራዊየተደረገነው ፡፡በትላልቅፕሮጀክቶችእድገትንማስደገፍየራሱየሆኑጠንካራጎኖችያሉትንያህልድክመትምአለውአንዱከላይእንደጠቀስኩትፕሮጀክቶቹየሚጠይቁትግዙፍፋይናንስማሰባሰብራሱንየቻለፈተናሲሆንበብድርቢገኝእንኳንጋብካልተደረገሃገርንበአጭርግዜውስጥግዙፍእዳውስጥሊከትየሚችልነው ፡፡በሌላበኩልደግሞፕሮጀክቶቹበትክክልከተጠናቀቁለረጅምግዜሃገርንሊጠቅሙየሚችሉመሂናቸውጠንካራጎናቸውነው ፡፡
በተለይምየዋጋግሽበትበሚንበርበትወቅትትላልቅፕሮጀክቶችከፍተኛወጪየሚወጣባቸውእንደመሆናቸውመጠንየዋጋግሽበትንየማባባስናየውጭምንዛሪእጥረትንበማባባስበኩልሚናሊኖራቸውይችላል ፡፡ትላልቅፕሮጀክቶችመንግስታትንበህዝብእንዲወደዱራሳቸውንየሚያሳዩበትእድልንየሚሰጥነው ፡፡ ነገርግንከትላልቅፕሮጀክቶችባሻገርግንምጣኔሃብታዊማሻሻያዎችንበማድረግየበለጠዘላቂእድገትንማፋጠንየሚቻልበትየፖሊሲእድልአለ ፡፡
ምንምእንኳንከወጪንግድገቢአስፈላጊውየዶላርገቢይገኛልተብሎቢታሰብምይህንማሳካትአልተቻለም ፡፡ ከወጪንግድየሚገኘው 3 ቢሊየንዶላርብቻሲሆንነገርግንየሃገሪቱየውጭምንዛሪፍላጎት 16 ቢሊየንዶላርመድረሱአሳሳቢሲሆንበዚህመሃከል ያለው የ13 ቢሊየንዶላርክፍተትንፍላጎትንለመሙላትየወጪንግዱብቻውንሊያሟላውእንዳልቻለመረዳትይቻላል ፡፡ከሌሎችሃገራትልምድእንደምንረዳውየውጭምንዛሪእጥረትለመቅረፍበወጪንግድብቻመተማመንበቂስላልሆነበተለያዩዘርፎችአስተማማኝናቀጥተኛናቋሚየሆነየውጪኢንቨስትመንትመሳብአስፈላጊነው፤ በእርግጥይህኢንቨስትመንትበኢንዱስትሪውዘርፍእንዲሆንናየወጪንግድንእሚያጠናክርመሆንይጠበቅበታል፤ ነገርግንበበቂሁኔታመሳብአለመቻሉየወጭንግዱንበሚፈለገውደረጃላለማሳደግእንቅፋትሆኗል ፡፡ 
ግሽበትንበተመለከተየዋጋውድነትንለመቆጣጠርናብሎምዋጋዎችንለመቀነስያለውበርካታአማራጮችያሉቢሆንምአይኤምኤፍባወጣው መግለጫየኢትየጰዮጲያየውጭእዳ ጫናወደከፍተኛደረጃመድረሱንናይህምመሰረታዊሸቀጦችንወደሃገርውስጥለማስገባት እንደ ስንዴ ፤ ስኳርና ዘይት የመሳሰሉትንለማቅረብአስቸጋሪሁኔታንእንደፈጠረ ተገልጸዋል፡፡ አይኤምኤፍ በበኩሉ ባወጣውመግለጫኢትዮጲያንናታንዛንያንበከባድየእዳጫናውስጥእየገቡእንዳሉአስጠንቅቋል ፡፡
የውጭምንዛሪእጥረትመፈጠርየዋጋግሽበትንበማባባስአሉታዊአስተዋፅኦንአድርጓል ፡፡ይህምየፖሊሲማሻሻያንማድረግአስፈላጊሆኖተግኝቷል ፡፡ነገር ግን በዚህዘርፍፖሊሲአውጪዎችምንያህልዝግጁ ናቸው የሚል አግባብነትያለው ጥያቄ ቢነሳ ተገቢ ነው ፡፡ በፋይናንስ ዘርፍ በተለይም ማሻሻያዎችን ደፈር ብሎ ማድረግ አስፈላጊሲሆንየፋይናንስዘርፉንለውጭባንኮችናየፋይናንስተቋማትበመጠኑከፈትማድረግ አንዱ አማራጭ መሆኑን በርካታ የምጣኔ ሃብት ባለሙያዎች እየተናገሩ ይገኛሉ ፡፡ለውጭ ባንኮች ዘርፉ ዝም ተብሎ ባንዴ የሚከፈት ሳይሆን ቀስ በቀስ ለቀቅ እየተደገረገ የሚከፈት ነው ፡፡ ለምሳሌ ቻይና የውጭ ባንኮች ወደ ሃገሯ እንዲገቡ ስትፈቅድ በጀመሪያ ከሃገር ውስጥ ባንክ በጋር የጋራ ሽርክናን በመፍጠር እንጂ የውጭ ባንኩ ብቻውን ሊገባ አይችልም ፡፡ ቀስ በቀስ ግን ቻይና የውጭ ባንኮች ብቻቸውን ወደ ፋይናንስ ዘርፉ እንዲገቡ ፈቅደዋል ፤ በዚህም የምእራባውያንን ድጋፍ አግኝተውበታል ፡፡ በርግጥ የቻይና ሞዴል ሙሉ ለሙሉ ከኢትዮጲያ ጋር ተመሳሳይነውማለትአይደለም፡፡ ቻይናየፋይናንስዘርፍንበሰፊውመክፈትየጀመረችው የፕሬዝዳንት ትራምፕ ወደ ስልጣን ሲመጡ ከቻይና ጋር ያለውን የንግድ ጉድለት አስተካክላለሁ ስላሉ ኢኮኖሚዋን ዝግ አደረገች እንዳትባል ከፈት ማድረግጀምራለች ፤ነገርግንትራምፕበዚህሳይወሰኑበቻይናየአልሙኒየምናበብረትምርቶችላይማእቀብንጥያለሁብለዋል፡፡ነገርግንቻይናየቴሌኮምእናየፋይናንስዘርፏንክፍትማድረጓየዓለምየንገድድርጅትአነባል እንድትሆንና በንግድ እንድትበለፅግና ከፍተኛየውጭምንዛሬ በገቢን በማግኘት መልሳ ለአሜሪካ አበዳሪለመሆንአብቅቷታል ፡፡ ይህ እድል አሁን ቀጥሎ ተጠቃሚይሆናሉ፤ ተብለውየሚጠበቁትእንደኢትዮጲያያሉትየአፍሪካአገራት ናቸው ፡፡ከዚህ ለመረዳት የሚቻለው ስልታዊ በሆነ መንገድ ኢኮኖሚን ክፍት ማድረግ የበለጠ ተጠቃሚ እንደሚያደርግነው ፡፡በዚህ ዘርፍ ለዘብያለናአሁንካለውወቅታዊከሆነውእንቅቃሴአንጻርበተግባርየሚሰራንፖሊሲመከተልአማራጭመሆኑን ማስተዋልያስፈልጋል ፡፡


Sunday, April 29, 2018

የፍህ ስርአቱ ሲፈተሽ justice & legal system ethiooia

ፀሃፊው በስሜነህ ተረፈ
የፍትህ ስርአቱ ትኩረትን ይሻል
            መልካም አስተዳር ለማስፈን ዋነኛ መሳሪያ ከሆኑት ተቋማት መሃከል ፍርድ ቤቶች ዋነኞቹ ቢሆኑም ነገር ግን ህብረተሰቡ በሚጠበቅባቸው ደረጃ ላይ አለመሆናቸው የፍትህ አሰጣጡ ያለበትን ሁኔታ አሳሳቢ ደረጃ ላይ አድርሶታል ፤ ፍርድ ቤቶች ተገቢውን ፍትህ ለመስጠት ዝግጁ አለመሆናቸው በአሁኑ ሰአት በፍርድ ቤቶች አካባቢ የሚታየው የስነ ምግባር ውድቀት አሳሳቢ ደረጃ ላይ መድረሱን ማንም ፍርድ ቤት የሚመላለስ ሰው በቀላሉ የሚያስተውለው ሆኗል ፡፡ በከተማችን በሚገኙት ፍርድ ቤቶች አካባቢ የመዝገቦች መብዛት ፤ የቀጠሮ መርዘምና መደጋገም እንዲሁም የአቅም ማነስና በአጭሩ መቅጨት የሚቻሉ ጉዳዮች አለአግባብ ማንዛዛትና በዜጎች ንብረት መበላሸትና ውድመት እንዲደርስ ማድረግ ፤ የውሳኔዎች ጥራት መጓደል ፤ በተራዘመ ቀጠሮ ንብረቶች በማይገባው ተከራካሪ እጅ ለረጅም አመታት ያለ ውሳኔ መቆየት ፤ አርዝሞ በመቅጠር ማቆየት አንደኛው ወገን ማግኘት የማይገባውን ጥቅም እንዲያገኝ ማድረግና ሌላውን ወገን ተጎጂ ማደርግ አድሎአዊ አሰራር፤ እንደዚሁም የስነ ስርአት ህጎቹ የሚያዙዋቸውን አንቀፆችን አለመጠቀም እና ነገሩን ማሳጠር ሲቻል ነገር ግን ችላ ብሎ በማለፍ ጉዳዩን የሚጓትት አካሄድን መከተል የሚታዩ ጉልህ ጉድለቶች ይሆናሉ
            በአሁኑ ወቅት አንድ ዳኛ በፈለገው ቀን እያስረዘመ ቀጠሮን የሚሰጥ ሲሆን ነገር ግን ያለውሳኔ ለሚያጓትተው ጉዳይ ምንም ተጠያቂነት የለበትም ፡፡ ጠ / ፍ ቤቱ የጉዳዮች አስተዳደር መመርያ ማለትም የመዝገቦች አቀጣጠር መመርያ ይወጣል ቢባልም ወጥቶ ስራ ላይ አልዋለም ፡፡ የፍርድ ቤት ውሳኔ መጓተት ከሃገር ኢኮኖሚ ላይ ውድመትን እያስከተለ ሲሆን ፤ በስር ፍርድ ቤት አመራሮች ዘንድ የሚስተዋለው የስነ ምግባር ችግር በጠቅላይ ፍርድ ቤቱ የበላይ ሃላፊዎች ዘንድ ግንዛቤው ጨርሶ አለመኖር ፤ እንደዚሁም ዳኞችን ከኋላ በስልክ ይታዘዛሉ የሚልም የባለጉዳዮች ጥርጣሬ ያለ ሲሆን በፍትህ ስርአቱ ላይ ከምንግዜውም የወረደ የህዝብ አመኔታ መኖሩ ግን ወዴት እየሄድን ነው ያሰኛል ፡፡ ለዜጎች ፍትህ ያሰፍናል ተብሎ የሚታመንበት ተቋም ዜጎች ፍትህን እንዳያገኙ ዋነኛ ባላጋራ ሆኖ መነሳቱ አሳሳቢ ነው ፡፡ በፍ / ቤቶች ለፍትህ ቆመዋል የሚባሉ ተቋማት እንደመሆናቸው የሚታየው የተበላሸ አሰራር በብዙዎች የአስፈጻሚ መቤቶች እምብዛም የተለመደ አይደለም ፤ ይህም በመንግስት ላይ የአመኔታ እንዲሸረሸርና ህብረተሰቡ የትም ሄጄ መብቴን በትክክለኛው መንገድ ማስከበር አልችም የሚለው አስተሳሰብ በተለይም በወጣቱ ዘንድ ተስፋ መቁረጥን ሲፈጥር ወደ አመፅና ግርግር አገሪቷን ጨምሯል ፡፡  
            ከህዝብ ቅሬታዎችን የመቀበልና መፍትሄ የመስጠት ስልጣን በአዋጅ የተሰጠው የዳኞች አስተዳደር ጉባኤ ቢሆንም ጉባኤው ከህዝብ ለሚቀርቡለት ጥያቄዎ በይፋ ምላሽን ሲሰጥ አይታይም ፤ የዳኝነት በደሎች ፤ አድልኦ የመሳሰሉት ባለጉዳዮች ሲያጋጥሟቸው ለጉባኤው ያቀርባሉ ቢባልም ጉባኤው በወር አንዴ ብቻ የሚሰበሰብ ሲሆን አባላቶቹም በርካታ በሌላ መ / ቤቶች ውስጥ ስራ ያላቸው ስለሆነ ዋነኛው ስራቸው አይደለም፡፡ በሃገሪቱ በሞላ የሚቀርቡለትን ጉዳዮችን የሚመለከተው ጉባኤው በወር አንዴ ብቻ መሰብሰቡ በቂ ነው ወይ ሊባል ይችላል ፡፡፡
            በተለይም በፍርድ ቤት ንብረትን ማስለቀቅ በጣም ከባድ ከመሆኑም በላይ ለኪራይ ሰብሳቢነት በርን የከፈተ ሲሆን የመንግስትን ትኩረት የሚሻበት ደረጃ ላይ ደርሷል፤ ያለቀውን ጉዳይ አስከ ሰበር ችሎት ድረስ ያስቀርባል በማለት በተደጋጋሚ አፈጻጸም በማገድ በተደጋጋሚ በማከራከር ጉዳዮችን በማርዘም በባለጉዳዮች ላይ ይሄ ሃገራችን ነው ውይ ብለው እስከሚጠራጠሩ ድረስ ግፍ እየተፈፀመ ይገኛል  ፡፡ የንግድ ቤቶች አከራዮች እዚህ ላይ ጠንቀቅ እንዲሉ ምክሬን እሰጣለሁ በአሁኑ ወቅት የንግድ ቤት ጉዳይ ወደ ፍርድ ቤት ከገባ ቀላል የአከራይ ተከራይ ጉዳይ ቢሆንም እንኳን አመታትን ሳይፈጁ በቀላሉ ቤቶቹ የማይለቀቁ ሲሆን የመዝገብ ቤት ፀሃፊዎች ጭምር መዝገቡንና ባለጉዳዩን እንዲለዩት የሚደረግ ሲሆን ከፍተኛ ጉቦ የሚረጭበት ክርክር እንደሆነ በጠበቆች ጭምር በይፋ ይነገራል ፤ በመንግስት ደጋፊዎች በሆኑ ዘንድ ሳይቀር የዚህ አይነት ክርክሮችን ለመርታት ደህና ገንዘብ እንደሚያስፈልግ በይፋ እየተነገረ ይገኛል ፡፡
            በአንድ ወቅት አንድ የህግ ባለሙያ በጋዜጣ ላይ ከሰጡት መግለጫ እንደሰማሁት የዳኞች ሹመት ግልፅ አለመሆንና በጣም ወጣቶች መሆን በራሱ ችግር እንዳለው ሲለግፁ ሁሉም ደካማ ናቸው ባይባልም ነገር ግን የእድሜ ገደብ ቢንስ ወደ 30 አመት ከፍ ቢል ከእድሜ ተሞክሮ የተሻለ ዳኝነት ለመስጠት የሚስችል ሲሆን ባለጉዳዮች ሊያፍሩባቸው የሚችሉ ግለ ጉዳዮች ለምሳሌ የባልና የሚስት የውስጥ ገመና አይነት ክርክሮችን ለመረዳት እድሜ ያበሰለው ሰው ይመረጣል ተብሎ ይታሰባል ፡፡ የትምህርት ዝግጅት ብቻ ሳይሆን የዳኝነት ስራ በባህሪው የእድሜ ተሞክሮ የሚፈልግ ስለሆነ ነው ፡፡  
            ከዚህ ጋር ተያይዞ የዳኞች ደሞዝና ጥቅማጥቅም በመንግስት ጭማሪ እንዲደረግና ይህንንም ለማድረግ የበጀት እጥረት እንዳለ የጠቅላይ ፍ/ቤት ፕሬዝዳንት አቶ ዳኜ መላኩ በሚዲያ የገለፁ ሲሆን ጠቅላይ ፍ / ቤቱ የራሱ ቦታ እንደተሰጠው ተሰምቷል የቢሮ እጥረቱን የሚቀርፍለት ሲሆን የዚህ እነኚህ ጅምሮች የሚበረታቱ ናቸው ፡፡ ጠቅላዩ ፍርድ ቤቱ በኮምፒተር መረጃዎችን የመያዝ ፤ መዝገብ የመክፈትና ክፍያዎችን የመፈፀም በተመለከት ማሻሻሉ ፤ በበርካታ መስኮቶች ባለጉዳዮች ያለወረፋ ማስተናገድ መጀመሩ መልካም ቢሆንም  ነገር ግን አስፈላጊ የሆኑ መመሪያዎች አለመውጣታቸው በራሱ ችግርን እንደፈጠረ የጠቅላይ ፍርድ ቤቱ ሃላፊዎች በሚዲያ የተናገሩ ሲሆን አንድ ጉዳይ ወደ ይግባኝ ሲሄድ ያስቀርባል ወይስ አያስቀርብም የሚለው ግልፅ የሆነ መመሪያ አለመኖሩ በራሱ ችግርን እንደፈጠረ የስር ፍርድ ቤት በትክክል የፈረዳቸው ማለቅና መቆም ሲገባቸው ያስቀርባል ተብለው ውሳኔዎቹም ላይቀየሩ ነገር ግን የዜጎች ንብረት አፈጻጸም ታግዶ አለአግባብ እንደሚንከራተቱ ይታያል ፤ አንዳንዴ ደግሞ ሊያስቀርቡ የማይገቡ ሆነው ነገር ግን በአድላዊ አሰራር አፈጻጸማቸው ታግዶ ይቆይ ለሰበር ይቅረብ ተብለው ፣ ትክክለኛ የሆነው የስር ፍርድ ቤት ውሳኔዎች በግፍ ሲሻሩ ይስተዋላል ፤ ሌላ ግዜ ግልፅ ያልሆኑና የተምታቱ ውሳኔዎችን የፌ/ጠ/ፍ/ቤት ሰበር ችሎት ሲሰጥ ይታያል ፡፡ ይሁንና የሰበር ችሎት የመጨረሻው ይግባኝ ሰሚ ፍ/ ቤት ነው እንጂ ህገ መንግስታዊ ፍ / ቤት አለመሆኑ የሚታወቅ ፤ ነገር ግን በተደጋጋሚ ሰበር ችሎት እንደ ህገ መንግስታዊ ፍርድ ቤት ሆኖ ሲሰራም ይስተዋላል ፡፡ የፌ/ጠ/ ፍ/ ቤት ሰበር ችሎት ለስር ፍ / ቤት አስገዳጅ የሆኑ ሃያ በላይ ቅፆችን ያሳተመ ሲሆን ይህም የሚያሳየው በተለይም የፍትሃ ብሄር ህጉ ውስጥ በርካታ ግልፅ ያልሆኑ ነገሮች ስላሉ እነዛ ሰበር ችሎቱ አንዳንድ ግዜም እንደ ህግ አውጭ ፓርላማ ስራን እየሰራ ነው ማለት ይቻላል ነገር ግን ሰበር ችሎቱ በአንድ ወቅት የያዘውን ኣቋም በሌላ ግዜ መለወጥ መቻሉ ነው ከህግ አውጭው የሚለው ፤ ከዚህ ይልቅ ግን ሰበር አስገዳጅ የህግ ትርጉም የዚህን ያህል መዝገቦች መብዛታቸው በራሱ ህጉ መፈተሸና መሻሻል እንዳለበት አመላካች ነው ፤ ህጎቹ ግልፅ ቢሆኑ ኖሮ የዚህን ያህል የበዙ ጉዳዮች አስገዳጅ የህግ ትርጉም ባልተሰጠባቸው ነበረ ፡፡  
            ይህ ብቻ አይደለም ህግን የመተርጎም እንደ ህገ መንግስታዊ ፍ / ቤት ሆኖ ስልጣን የተሰጠው ለፌዴሬሽን ም/ ቤት መሆኑ በራሱ ለህግ አተረጓጎም ችግርን ፈጥሯል ፤ ፌ/ ም ቤት ራሱ የአስፈጻሚው የገዢው ፓርቲ አካል ሆኖ መልሶ ከፍ / ቤቶች በላይ ህግ ተርጓሚ መሆኑ ህገ መንግስታዊ ትርጉም ያስፈልጋቸዋል የሚባሉ ጉዳዮች ወደ ም/ቤቱ የሚሄዱ ሲሆን የህግ አውጭውን ፤ የአስፈጻሚውንና የህግ ተርጓሚ የመንግስት አካላት ስራን የሚያደበላልቅ ነው ፡፡ ከዚህም አልፎ በቅርቡ ስራውን የጀመረው የህገ መንግስታዊ አጣሪ ኮሚሽን የተባለው ተቋም ስራ መጀመሩ መልካም ሲሆን በርካታ የህግ ክፍተቶች ባሉት የፍትህ ስርአቱ ፍርደ ገምድል ውሳኔ ተወስኖባቸው አጣሪ ኮሚሽኑ ያስተካከላቸው እንዳሉ ይታወቃል ፤ ይሁንና ይህ ተቋም የበላይ ሃላፊዎቹ ፍርዱን የፈረደው ተቋም የጠ/ፍ / ቤት ሃላፊዎች መሆናቸው ራሱ ፍርድን የሰጠው ሰው መልሶ ቅሬታውን የሚያየው መሆኑ አሁንም የአጣሪ ኮሚሽኑን ነጻነቱንና ተጠያቂነት አጠያያቂ ያደርገዋል ፡፡ 
            ለመልካም አስተዳደር መጠናከር ዋነኛው የፍትህ ስርአቱን መፈተሸና የዳኝነት ስርአቱን በተደጋጋሚ ማሻሻል አስፈላጊ ቢሆንም በከፍተኛ የመንግስት አካላት ሳይቀር ተገቢውን ትኩረት አላገኘም ፡፡ አንዳንዶቹ ህጎች ከወጡ ረጅም አመታት ያለፋቸውና ለአሁኑ ዘመን እንዲያሰሩ በሚገባ መሻሻል የነበረባቸው ቢሆንም ሳይሻሻሉ ለበርካታ አስርት አመታት የዘለቁ እንዲሁም ከህገ መንግስቱ በላይ እድሜ ያላቸውና በስራ ላይ ካለው ህገ መንግስት ጭምር ጋር የሚጣረሱ ሆነው ሳለ ነገር አሁንም እየተሰራባቸው ነው ለምሳሌ ከ60 አመታት በፊት የወጣው የፍትሃ ብሄር ህጉ በርካታ ክፍተቶች ያሉበትና ጉዳዮች በቀላሉ እንዲቋጩ የሚያደርግ ካለመሆኑም በላይ ዜጎች በቀላሉ በፖሊስ ሊያልቁ የሚችሉና የሚታወቁ ነገሮች ላይ አመታት በይግባኝ እንዲጓተቱ የሚያደርግና ለዳኛው ከሚሰጠው ሰፊ ስልጣን አንጻር ለኪራይ ሰብሳቢነት በርን የከፈተ ነው ፡፡ የንግድ ህጉም ቢሆን የቆየ ሲሆንም እሱንም ለማሻሻል ስራ እየተሰራ እንደሆነ በጠቅላይ አቃቤ ህግ የተገለፀ ቢሆንም ተሻሽሎ አልወጣም፡፡ አሁን ሃገሪቱ ካለችበት ፈጣን የኢኮኖሚ እድገት አንጻር ህጎች ከዘመኑ ጋር መሄድ የሚጠበቅባቸው ቢሆንም ነገር ይህ ሲሆን አይታይም ፡፡
            ፍትህ ስርአቱ የሚወስናቸው ውሳኔዎች በሃገሪቱ የፖለቲካ ጉዞ ላይ መልካምም ሆነ አሉታዊ ተፅእኖ ያለው ሲሆን ቀጥተኛ የፖለቲካ አስተዳደሩን ህልውና በበጎም ይሁን በመጥፎ ይወስናል ፡፡ በሃይለስላሴ ግዜ በ1953 ዓ.ም. ተሞክሮ በከሸፈው የጄኔራል መንግስቱ ንዋይ መፈንቅለ መንግስት ወቅት ጄኔራሉ ለምን መፈንቅለ መንግስት ሊያካሂዱ እንደተነሳሱ ፍ / ቤት ቀርበው በተናገሩት ንግግግር ላይ ህዝቡ በትክል ዳኝነትን እንደማያገኝ እስከ 20 እና 25 አመት ድረስ ፍርድ ቤት ሲመላለስ እንደሚኖር እንደዚሁም በንብረት፤ በመሬት ክርክሮች አስርት አመታትን በሚፈጅ የፍርድ ቤት ሙግት ቤተሰብ እንደሚፈራርስ፤ ልጆች እንደሚበታተኑ እንደዚሁም ለንብረቱ ሲባል በተከራካሪው ወገን ላይ እስከ መገደልና ንብረቱን በህግ ማስመለስ በሚያቅተው ወቅት በሰውየው ህይወት ጭምር አደጋ እንደሚጋረጥ ፤ ይህ ሁሉ ሲሆን መቁዋጫ በሌለው የአመታት ሙግት ህዝቡ ሲሰቃይ ማየታቸውንና ንጉሰ ነገስቱም ለማሻሻል ጥረት አለማድረጋቸውን ነገር ግን ህብረተሰቡ ለህግ በነበረው አክብሮት ግን ለአመታት ይመላለስ እንደነበረ ተናግረዋል ፡፡ የዙፋን ችሎት ተብሎ ዛሬ እንዳለው የሰበር ችሎት የነበረ ቢሆንም ነገር ግን ችሎቱ ላይ ይቀመጡ የነበሩት ራሳቸው ንጉሰ ነገስቱ ስለነበሩ እርሳቸው ካለባቸው የመንግስት ስራ ጫና የተነሳ ጉዳዩ ዙፋን ችሎት ደረጃ ለመድረስ አመታትን ይፈጅ እንደነበረ መገመት ይቻላል፤ እንደዚሁም ንጉሰ ነገስቱ አስፈጻሚው አካል ሆነው መልሰው ህግ ተርጓሚ ዳኛ መሆናቸው ራሱ የህግ ጥያቄን ሊያስነሳ ይችላል ፡፡ የፍትህ በወቅቱ አለመስፈን የቤተሰብ ብሎም የህብረተሰቡ ሰላም እንደሚያናጋ አሁን በቅርቡ በሃገራችን ያየናቸው አስፈሪ የህዝብ ተወቃውሞ እንቅስቃሴዎች አስረጂዎች ናቸው ፡፡     
            በየትም ሃገር እንደሚደረገው ሁሉ አንድ የፍትህ ስርአት ውስጡ ችግሮች ካሉበት መሻሻል እንዳለበት የታወቀ ሲሆን መንግስታት የህዝብን ጥያቄዎችንና የመልካም አስተዳደር ጉዳዮችን ለመመለስ በፍትህ ስርአታቸው ላይ ትኩረትን በማድረግ በየጊዜው አዳዲስ ህጎችን በማውጣ ህጎቻቸውን በተደጋጋሚ ሲያሻሽሉ የምንሰማ ቢሆንም በሃራችን ግን አንድ ህግ አላሰራ ማለቱና መሻሻል እንደሚያስፈልገው እየታወቀ ሳይሻሻል ለረጅም ጊዜ እንዲሰራበት በማድረግ ብዙ ችግርን ከፈጠረ በሁዋላ ወደ ማሻሻል ሲገባ ይስተዋላል ፡፡ አንድ መንግስት ስራው አስተዳደር ብቻ ሳይሆን ጥናት እያደረገ ነባሮቹን ማሻሻልና አዲስ ህጎችን ማውጣት ነው በተለይም የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ዋነኛው ስራው ህጎቹን ማውጣት ለህግ ተርጓሚው አሻሚ ያልሆኑ ህጎችን መደንገግ ነው ፡፡ ጭራሽ ህችን ካለማውጣት ደግሞ አንድ ህግ ወጥቶ ተሰርቶበት በስራ ሂደት ያለው ድከመት ታይቶ ማሻሻል የበለጠ ተመራጭ ነው ፡፡ እኛ ግን ህግን ለማውጣትም ሆነ ለማሻሻል የምንፈራ እንመስላልን ፤ ምናልባት በመንግስት በኩል እነኚህ ነጻነትን የሚገድቡ ህጎች በቀደሙት መንግስታት ዘመን የወጡ ስለሆነ ነገር ግን ባሻሽላቸው ስልጣኔን የተወሰነው ይቀንስብኛል የሚል ስጋት ሊኖረው ይችላል ብለን ብናስብ እንኩዋን ፤ አሁን ባለው በሃራችን ተጨባጭ ሁኔታ ለመንግስት ስጋት የሚሆነው የመልካም አስተዳር አለመስፈን ስለሆነ የበለጠ ዋጋን እንደሚያስከፍል መረዳት ይቻላል ፡፡ እንደውም መንግስት አሁን ካለው አሳሳቢ ከሆነው የሃገሪቱ ወቅታዊ ሁኔታ በመነሳት ህዝቡ ፈጣን ምላሽንና መሻሻልን የሚጠብቅ በመሆኑ  የህግ ክፍተት ያለባቸውን ህግጋት በባትሪ  ብርሃን እየፈለገ ማሻሻል ያለበት ወሳኝ ወቅት ላይ እንገኛለን ፡፡
            ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር አቢይ ክፍተት ያለባቸውን ህጎች እንደሚያሻሽሉ ፤ እንደዚሁም በተደጋጋሚ የህዝብ ቅሬታ የሚቀርብባቸውን የመንግስት መስሪያ ቤት ሃላፊዎችን እንደ የአመራር ለውጥ እንደሚያደርጉ መግለጻቸው የሚታወስ ሲሆን ፍርድ ቤቶች ዋነኛ የህዝብ ቅሬታ ማእከል ከሆኑ ቆየት ብሏል ፤ እንደዚሁም ብሄራዊ ባንክ ቅሬታ የሚቀርብበት ቢሆንም እነኚህ ሁለት ወሳኝ ተቋማት በጠቅላይ ሚ/ሩ የመጀመሪያ ሹመት የአመራር ለውጥ ሳይደረግባቸው ቀርተዋል፡፡
            አንድ ሰሞን ዋነኛ የህግ ክፍተት ከሚታይባቸው ዘርፎች አንዱ የሆነው የአከራይ ተከራይ ፤ የሪል ስቴትና የቤቶች ግዢና መግዛትን የሚመለከት ህግ ይወጣል ቢባልም ሊወጣ ጫፍ ደርሶ ሲያበቃ በማይታወቅ ምክንያት ህጉ ሳይወጣ ቀርቷል ፡፡ መንግስት ለዜጎች ለአመታት ደክመው የሰሯቸውን ቤቶች ንብረት ለድርድር የማይቀርብ የህግ ከለላና ጥበቃ ማድረግ አለበት ፡፡ አሁን በስራ ላይ ያለው የፍትሃ ብሄር ህግ ይህንን ለማድረግ የሚያስችል ካለመሆኑም በላይ አንድ አይነት አለመግባባት ቢፈጠር የዜጎች ውል የመዋዋል መብትንና ከውል የሚመነጭ መብታቸውን ለማስከበር ፤ እንደዚሁም ግዴታዎችን ለማስፈጸም አስቸጋሪና የተንዛዛ የአመታት የፍርድ ቤት ምልልስን የሚፈጥር ነው ፡፡ ለምሳሌ አንድ ሰው ኮንዶሚኒየም ቤት ቢገዛና ከሻጩ ጋር አለመግባባት ቢፈጠር ነገሩን ለማስተካከል ወደ ህግ ክርክር ከሄደ ውሳኔ ለማግኘት አመታትን የሚወስድ ነው ፡፡ ይህ አዋጅ ለዚህ አይነት ጉዳዮች ፍቱን መድሃኒት ሊሆን የሚችል የነበረ ሲሆን መዘግየቱ ግን ተገቢ አለመሆኑን መረዳት ይቻላል ፤ ይህን በመፍራት ብዙዎች ከመግዛትና መሸጥ ሲታቀቡ ታይቷል ፡፡  በነባሩ የፍትሃ ብሄር ህግ መሰረት አንድ ሰው ተከራይ ሆኖ የሰው ቤት ገብቶ ነገር ግን ካርታና ሰነድ ለውጦ የቤት ባለቤት የሚሆንበት ሰፊ የህግ ክፍተት ያለ ሲሆን እንደዚሁም የሪል ስቴት ኩባንያዎች ቤቶችን ለማስራት ከደንበኞቻቸው ገንዘብን ከሰበሰቡ በሁዋላ አንዳንዶቹ እጅግ ዘግይተው ቤቱን ሰርተው የሚያስረክቡ ሲሆን አንዳንዶቹ ደግሞ ጭራሽ ገንዘቡን በማበባከን ቤት ገዢዎችን በነጻ እንዲወጡ ያደረጉ እንዳሉ በሚዲያ የምንሰማው ጉዳይ ነው ፡፡ በነባሩ የፍትሃ ብሄር ህግ ሪል እስቴት የሚባለው ቃሉ ራሱ የማይታወቅ ሲሆን በአንድ የሪል ስቴት ቤት ገዢና ሻጭ መሃከል አለመግባባት ቢፈጠር በተለይ ቤት ሰርቼ አስረክባለሁ ብሎ ገንዘብ የተከፈለው አካል ተጠያቂ የሚሆንበት የህግ አሰራርም ሆነ የህግ ማእቀፍ ወይም መመሪያም ሆነ አዋጅ የለም ፡፡ በአንድ የሪል ስቴት ኩባንያና በደንበኞቹ መሃከል በተፈጠረ አለመግባባት ላይ አንዱ ደንበኛ ወደ ፍርድ ቤት መሄድ የለብንም ሲል ተሰምቷል ይህም ሪል እስቴት ግልፅ የሆነ አዋጅ ስለሌውና በፍትህ ስርአቱ ላይ አመኔታ ባለመኖሩ ንብረቱ በአፈጻጸም ታግዶ በይግባኝ ለአስር አመታት ሊቀጥል ስለሚችል ባለው ፍራቻ ነው ፤እነዚህ ከብዙ በጥቂቱ ያሉ የህግ ክፍተቶች ናቸው ፡፡

            ነገር ግን ለዚህ ሁሊ መፍትሄ ሊሆን ይችል የነበረው የሪል ስቴት አዋጅን ማውጣት ቢሆንም አዋጁ እንደገና እንዲስተካከል በሚል ሳይወጣ ቀርቷል ፡፡ የቀድሞው ጠቅላይ ሚ/ር መልካም አስተዳርን ለማስፈን ጥረት አድርገው የነበረ ቢሆንም ነገር ግን በፍትህ ስርአቱ ላይ ትኩረትን አለማድረጋቸው ሳይሳካላቸው እንዲቀር ምክንያት ሆኗል ፡፡ ከዚህ ቀደም በአቶ ለማ መገርሳ የተመራው ኦህዴድ በኦሮሚያ ክልል የፍትህ ስርአቱን መልሶ ያዋቀረ ሲሆን ይህም በፌደራል ቢደገም መልካም ነው ማለት ይቻላል ፡፡ የአሁኑ አዲሱ ጠቅላይ ሚ/ ር የህግ ክፍተቶችን በመድፍን ወደ ስራ በመግባት እንደዚሁም መቼም ቢሆን ከፍትህ ስርአቱ ላይ አይናቸውን መንቀል የለባቸውም ፤ ለቀድሞው ጠ / ሚር አስተዳደር አለመሳካትና የህዝብ ቅሬታ ምንጮች በመሆን ፍ / ቤቶች ዋነኛ አሉታዊ አውዳሚ ሚናን መጫወታቸው የአደባባይ ሚስጥር ነው ፡፡

Wednesday, December 16, 2015

Ethiopian law constitution

Ethiopian Constitution and Courts Law የኢትዮጲያ ህግና ህገ መንግስት - http://wp.me/p39p0v-8j

Saturday, March 14, 2015

Property Rights In Ethiopian Law የኢትዮጲያ ህግና የንብረት ባለቤትነት (Property Right) መብት አፈፃፀም

 

            አንድ የፍርድ ቤት ሙግት በርካታ ወራትን ብሎም አመታትን የሚፈጅ ሲሆን ይህም ማለት ይህ ጉዳይ ፍርድ   ቤት ይዞታል በሚል ብቻ እውነቱ እስከሚወጣ ድረስ አመታትን መፍጀቱ የንብረት ባለቤትነት መብትን ህጉ በአግባቡ ማስከር ችሏል ወይ ? የሚል ጥያቄ ቢነሳ መልካም ነው ፡፡ በሃገራችን እንደሚታወቀው የፍርድ ቤት ሙግት በቀላሉ የማያልቅ ሲሆን በቀላሉ ወረዳዎች ወይንም ባስ ካለም ክፍለ ከተማዎች መፍትሄ ሊሰጡት የሚገችሉት ጉዳይ አመታትን ሰዎችን ሲያመላልስ ይስተዋላል ፡፡

          አንዱ መዋእለ ንዋይን ለማበረታታት ከሚመከሩት የተመቻቹ ሁኔታዎች አንዱ የንብረት ባለቤትነት (Property Right) መብትን ማስከበር ሲሆን በምእራባውያን የምጣኔ - ሐብት ባለሙያዎወች እንደተጠናው ከሆነ ለአፍሪካ ኢንቨስትመንትን አግባቡና  በበቂ ላለመሳቧ ዋነኛው ምክንያት የንብረት ባለቤትነት መብት በበቂ አለመከበሩ ነው ይላል ፡፡

          አንድ መዋእለ ንዋይ አፍሳሽ አንድ የውጭ ሃገር ሄዶ ገንዘቡን ሲያፈስ የሚያፈሰውን ገንዘብ ሲፈልገው መልሶ ማውጣት ሚፈልግበት በማንኛውም ሰዓት ላይ ማውጣትን የሚፈልግ ሲሆን የንብረት መብት (Property Right) በአግባቡ የማይከበርባቸው ሃገራት የውጭ መዋእለ ንዋይን የማግኘት እድላቸው በጣም ጠባብ ነው የሚሆነው ፡፡  ይህም አወዛጋቢ በሚሆንበት ወቅት የሚከበር ፍርድ ቤቶች አማካይነት በተፋጠነና በተከራካሪ ወገኖች ላይ የማያስፈልግ ወጭንና ኪሳራን በማያስከትል ሁኔታ በአንዱ ኪሳራ ሌላኛው አለአግባብ በማይጠቀምበት ሁኔታ መሆን አለበት ፣ የነገሩ መንዛዛት አንደኛው ወገን በአንደኛው ኪሳራ አለአግባብ እንዲጠቀም የሚያደርግ ሲሆን ፣ ይህ ካልሆነ ደግሞ በሁለቱም ወገኖች ላይ ከባድ ኪሳራንና መጓተትን ያስከትላል ፡፡ ለምሳሌ በእርስ በርስ ጦርነት የምትታመሰው ሶማልያን እናስብ ፤ አንድ የውጭ ሃገር ኢንቬስተር ሶማልያ ሄዶ መዋእለ ንዋዩን እንደማፍሰስ ብለን ብናስብ አንድ ባለሃብት እርዳታ አድርጎ ቢሰጠው ይሻለኛል ፣ ዝም ብዬ ሄጄ ገንዘቤን ከማፈስና ከምነጠቅ ብሎ ነው እሚያስበው ፣ ስለዚህ ሶማልያ መዋእለ ንዋይ የማግኘት እድሏ አነናሳ መሆኑ ግልፅ ነው ፡፡

          በአፍሪካ የንብረት ባቤትት መብት በአግባቡ የማይከበር ሲሆን ለኢንቨስትመንት አስፈላጊ የሆነ መሬት ያለ በቂ ሰነድ የሚያዝ ሲሆን መዋእለ ንዋይን ለማፍሰስና ለማሳደግም ሆነ ለማሻሻል አስቸጋሪ ሲሆን አድርጎታል ብለው የውጭ ባለሙያዎች ይናገራሉ ፡፡ ከዚህ ተጨማሪ ግን ፍርድ ቤቶች ጠንካራ ሆነው የንብረት ባለቤት ህጉን ለማስከበር ፈጣንና ወጪ ቆጣቢ በሆነ መንገድ መፍታት ካልቻሉ ረጅም ግዜን መውሰዱ መዋእለ ንዋይን ከማረታታት አንፃር አሉታዊ ጎን ይኖረዋል ፡፡ ለምሳሌ አከራይና ተከራይ መሐከል ያለ ክርክር አመታትን ሊወስድ ይችላል በዚህም ምክንያት አከራዩ ፣ ክርክሩ ቤቱ ተይዞት ከሆነ የሚካሄደው ቤቱን እስከሚያስለቅቅ ድረስ የሚደርስበትን ኪሳራን ከውል ውጭ ጉዳት ደርሶብኛል በሚል ሌላ መዝግብ በመክፈት ድጋሚ ከሶ ብቻ ነው ማስከፈል የሚችለው ፡፡ ይህ ራሱ ደግሞ ከውል ውጭ ምን ያህል ነው የደረስብህ ኪሳራ የሚለው ለዳኝነት ቁልጭ ያለ ባለመሆኑ ምክንያት አሻሚ  ስለሚሆን ከውል ውጭ ጉዳት ለደረሰበት ወገን አርኪ ላይሆን ይችላል ፡፡ ከዚህም በተጨማሪም ጉዳቱ ለደረሰት ወገን የደረሰበት ጉዳት ሌላ ተጨማሪ ወጮጪን ፣ የጠበቃ አበልን የሚያስወጣው ሲሆን ጉዳቱ የበዛ ነው የሚሆነው ፡፡

          የኢንቨስትመንት አዋጁ እንደሚደነግገው ከዚህ ቀደም አንድ የውጭ ሃገር ዜጋ ኢትዮጲያ ውስጥ ቤት መግዛትም ሆነ መስራት የማይችል ሲሆን ነገር ግን የዚህ አዋጅ መሰረት ግን ኢንቨስተሩ ቤት ለመስራት ይፈቀድለታል ፡፡ ለምሳሌ በ2004 ዓ.ም. የወጣው የሊዝ አዋጁን ብንወስድ አዋጁ የወጣትበት ዋነኛው ምክንያት የትራንስፎርሜሽን እቅዱን ማሳካት የሚል ሲሆን ፣ የግል የንብረት ባለቤትነት መብትን ይጋፋል በሚል በህግ ባለሙያዎች የተተቸ ሲሆን ነገር ግን አዋጁ የወጣበት አላማ ግን መንፈሱን መረዳት ይቻላል ፡፡