Wednesday, November 7, 2018

privatisation process in Ethiopia

privatization ወይም የልማት ድርጅቶችን ወደ ግል የማዛወር ሂደት ምን መምሰል አለበት ? ፦

ሲጀመር ያክስዮን ግብይትን እሚያቀላጥፍ ተቁዋም በሌለበት ሁኔታ ምንም እንኩዋን
ecx ያክስዮን ግብይት እንዲያካሂድ የተሻሻለው አዋጅ ቢፈቅድለትም እና  የህግ ምእቀፍ ቢዘጋጅለትም ማገበያየት አልጀምረም። ያክስዮን ግብይት የሚዛወሩትን የልማት ድርጅቶችን የሚከታተሉ በርካታ ቦርዶች ቢቁዋቁዋሙም ነገረ ግን  ብቁዋቁዋቃምም ከንግዱ ማህበረሰብ አባላት ቦርድ አልተሾመም ብዙዎቹ ታዋቂ ሰዎችና የፖለቲካ ስዎች ሲሆኑ እነኝህም በየዘርፉ ባለሙያዎች አለመሆናቸው ይታወቃል። ባለሙያዎች አይደሉም። 
ካክስዮን ገበያ በሁዋላ ያክስዮን ግብይት ተቆጣጣሪ መ /ቤት መቃዋቃዋም አለበት ። ቦርድ ላይ የተሰየሙት ፥ይሁንና ግን የፖለቲካ መሪዎቹ ይህንን ዝውውር ለመፈፀም የሚያስችል አቅም ያላቸው አይመስልም አማካሪ ካልቀጠሩ በስተቀረ።  በሌላ ሃገር ቢሆን አማካሪዎችን በዘርፉ መቅጠር አማራጭ ነው የውጭም ሆነ ያገር ውስጥ አማካሪዎችን ቀጥሮ ማሰራት አስፈላጊ ነው ። ሌላው( policy flexibility) አስፈላጊ ሲሆን የዚህን ያህል ግዝፈትና ኣይነት ያለውን ሪፎርም ለማድረግ የተሙዋልስ ወይም።ምሉዕ የሆነ የፖሊሲ ማሻሻያ ማእቀፍን መዘርጋት ያስፈልጋል ግማሹን አሻሽዬ ግማሹን አላሻሽልም ማለት አይቻልም።  ከፊል አሻሽላለሁኝ ከፊሉን ደግሞ በነበረው አስቀጥላለሁ የሚለው የመንግስት ፖሊሲ የሚያስኬድ አይመስልም። ለዚህም ይመስላል ትላልቆቹን የልማት ድርጅቶችን ወደ ግል አዛውራለሁ ቢልም መንግስት ቀጣይ በምን መንገድ ነው እሚዛወሩት ? ዝውውር ከመጀመሩ በፊትስ የሚያስፈልጉት አዳዲስ ተቆጣጣሪ ተቁዋማት እነማን ናቸው ? መሻሻል ወይም እንደ አዲስ መውጣት ያለባቸው የህግ ማእቀፍስ ምን መምሰል አለበት እሚለው ፍኖተ ካርታ roadmap ያለው አይመስልም።

"የስራ ፈጠራ "፦

መንግስት የስራ ፈጠራ ኮሚሽን አቁዋቁማል ይህ መልካም ሲሆን ስራ ፈጠራ በትእዛዝ እሚፈጠር ሳይሆን የፖሊሲ መሳሪያዎችን( policiy) instruments መጠቀምን ይጠይቃል። በተለይም እብዛኛው የሃገሪቱ ሃብት በመንግስት የልማት ድርጅቶች በተያዘበት ሁኔታ እንዲሁም እንደ መብራት ሃይል ያሉት ከመንግስት ባንኮች ከፍተኛ ብድርን በወሰዱበት ሁኔታ የግሉ ክፍለ ኢኮኖሚን  crowed out በማድረጋቸው ወይንም ከውድድሩ ውጭ ማድረጋቸው የግሉ ዘርፍ በበቂ ሳያድግ ለዘመናት እንዲቀጭጭ አድርጎአል።

Tuesday, November 6, 2018

justice system ethiopia



የኢትዮፒያ የፍትህ ስርአት የፍትህ ሥርአት ማሻሻያ  
ፀሃፊው ስሜነህ ተረፈ
የቀድሞው ጠቅላይ / መልካም አስተዳርን ለማስፈን ጥረት አድርገው የነበረ ቢሆንም ነገር ግን በፍትህ ስርአቱ ላይ ትኩረትን አለማድረጋቸው ሳይሳካላቸው እንዲቀር ምክንያት ሆኗል ፡፡ ከዚህ ቀደም በአቶ ለማ መገርሳ የተመራው ኦህዴድ በኦሮሚያ ክልል የፍትህ ስርአቱን መልሶ ያዋቀረ ሲሆን ይህም በፌደራል ቢደገም መልካም ነው ሲባል ነበር ፡፡ የአሁኑ ጠቅላይ / ዶ/ር አብይ የህግ ክፍተቶችን በመድፍን ወደ ስራ በመግባት ነበረባቸው ተብሎ በተደጋጋሚ ሲነሳ የነበረ ሲሆን እንደዚሁም መልካም አስተዳደርን ለመድፈን መቼም ቢሆን ከፍትህ ስርአቱ ላይ አይናቸውን መንቀል የለባቸውም ለቀድሞው / ሚር አቶ ሃይለማርያም አስተዳደር አለመሳካትና የህዝብ ቅሬታ ምንጮች በመሆን / ቤቶች ዋነኛ አሉታዊ አውዳሚ ሚናን መጫወታቸው የአደባባይ ሚስጥር ነው
በፌደራል ደረጃ በጉጉት ሲጠበቅ የነበረው የፍትህ ስርአት ማሻሻያ እንደተጀመረ / ቤት አመራሮችን በመተካት ተጀምረዋል። እርምጃው የዘገየ ቢሆንም ለውጡ ግን አዋጆችን በማሻሻል መታገዝ አለበት በተለይም የዳኞች አስተዳደር ጉባኤ አዋጅ ሳይውል ሳያድር ሊሻሻል ይገባዋል። ይህ አዋጅ ይሻሻላል ጥፋትን የፈፀሙ ዳኞችን እስከ ወንጀል ድረስ ለመጠየቅ የሚያስችል ነው ተብሎ በአቶ ዳኜ መላኩ ተነግሮ የነበረ ቢሆንም የት እንደደረሰ አይታወቅም አዋጁ።
አመራር በመለወጥ ብቻ ሳይወሰን 60 አመታት ያህል የቆዩትን የፍትሃ ብሄርና የስ//ህጉ እንዲሁም የወንጀለኛ መቅጫ የስ//ህጉ መሻሻል የሚገባቸው ሲሆን አዳዲስ መውጣት ያለባቸውም ማውጣት ለፍትህ አሰጣጥ አመቺ ያልሆኑ ነባር  ህጎችን መፈተሽ ያስፈልጋል። እንዲሁም ያመራር ለውጡ ወደ ታችኛው /ቤቶች አመራሮች ማለትም የመ/ ድረጃና ከፍተኛ /ቤት አመራሮች በነካ እጃቸው ይለወጡ።
/ሚር / አብይና አዲሲቷ የጠ/ፍ ቤት ፕ/ት በነካ እጃቸው ወደ ታች ያለው የስር ፍርድ ቤት አመራሮችን ማንሳት ይገባቸዋል ። የፍርድ ቤቶች ዳኝነት ተበላሽቶ የከፋ ደረጃ የደረሰው ባቶ ተገኔ ጌታነህ የጠ/ ቤት / በነበሩበት ወቅት ሲሆን በእርሳቸው የፕ/ትነት ዘመን በርካታ ፍርደ ገምድል ውሳኔዎች ተወስነዋል በርካቶችም በሙስና የተነካኩበትና ተጠያቂነት የጠፋበት ሁኔታ ነበረ። ከእርሳቸው በሁዋላ የተሾሙት አቶ ዳኜ መላኩም / ቤቱን ለማሻሻል ጥረትን አድርገዋል የጠ/ ቤቱ ፕሬዝዳንቶቹ ጥቅማ ጥቅምም እጅጉን ተሻሽሎአል ይሁን እንጂ አቶ ዳኜ በርካታ ቅሬታ የሚቀርብባቸውን የስር /ቤት አመራሮችን አልነኩም ስለዚህ የእርሳቸው ጥረት የሚፈለገውን ለውጥ ሳያመጣ ቀርቶአል። የአሁኑዋ / / መአዛ አሸናፊም በቶሎ የስር /ቤት አመራሮችን በማንሳት ስራቸውን መጀመር አለባቸው አለበለዝያ ከላይ የእርሳቸው ጥረት ብቻውን ለውጥን አያመጣም። አዋጆችን ማሻሻል በእጅጉ አስፈላጊ ሲሆን ይሻሻላሉ የተባሉ አዋጆችም በፍጥነት መሻሻል አለባቸው ፡፡
ይህ ብቻ አይደለም ህግን የመተርጎም እንደ ህገ መንግስታዊ / ቤት ሆኖ ስልጣን የተሰጠው ለፌዴሬሽን / ቤት መሆኑ በራሱ ለህግ አተረጓጎም ችግርን ፈጥሯል ፌዴሬሽን ም/ ቤት ራሱ የአስፈጻሚው የገዢው ፓርቲ አካል ሆኖ መልሶ ከፍ / ቤቶች በላይ ህግ ተርጓሚ መሆኑ ህገ መንግስታዊ ትርጉም ያስፈልጋቸዋል የሚባሉ ጉዳዮች ወደ /ቤቱ የሚሄዱ ሲሆን የህግ አውጭውን የአስፈጻሚውንና የህግ ተርጓሚ የመንግስት አካላት ስራን የሚያደበላልቅ ነው ፡፡ ከዚህም አልፎ ስራውን የጀመረው የህገ መንግስታዊ አጣሪ ኮሚሽን የተባለው ተቋም ስራ መጀመሩ መልካም ሲሆን በርካታ የህግ ክፍተቶች ባሉት የፍትህ ስርአቱ ፍርደ ገምድል ውሳኔ ተወስኖባቸው አጣሪ ኮሚሽኑ ያስተካከላቸው እንዳሉ ይታወቃል ይሁንና ይህ ተቋም የበላይ ሃላፊዎቹ ፍርዱን የፈረደው ተቋም የጠ/ / ቤት ሃላፊዎች መሆናቸው ራሱ ፍርድን የሰጠው ሰው መልሶ ቅሬታውን የሚያየው መሆኑ አሁንም የአጣሪ ኮሚሽኑን ነጻነቱንና ተጠያቂነት አጠያያቂ ያደርገዋል ስለዚህ ይህ ሁሉ ጉዳይ የአዋጆች መሻሻልንና የአዲሲቱዋ ፕሬዝዳንት ወ/ሮ መአዛ አሸናፊ የቤት ስራ ይሆናል ማለት ነው ፡፡